የእኔ ፡ ነገር (Yenie Neger) - መስከረም ፡ ጌቱ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
መስከረም ፡ ጌቱ
(Meskerem Getu)

Meskerem Getu 1.jpg


(1)

እከተልሃለሁ
(Eketelehalehu)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፭ (2012)
ቁጥር (Track):

(1)

ርዝመት (Len.): 5:15
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የመስከረም ፡ ጌቱ ፡ አልበሞች
(Albums by Meskerem Getu)

አዝ፦ የእኔን ፡ ነገር ፡ የእኔን ፡ ጉዳይ
የያዘልኝ ፡ ጌታ ፡ አለ ፡ ከሰማይ (፪x)

ማደሪያው ፡ ልግባና
ላምልከው ፡ አንስቼ ፡ በገና (፪x)

የማማርረው ፡ አልሞላም ፡ ብዬ
ስሙን ፡ ላወድስ ፡ ሀዘኔን ፡ ጥዬ
ቢጐድልም ፡ እንኳን ፡ ወይኑ ፡ በለሱ
በዚህ ፡ አይለካም ፡ ጌታ ፡ ነው ፡ እርሱ

ጌታ ፡ ነው (፫x) ፡ ጌታ
ላመስግነው ፡ ሳለይ ፡ ሁኔታ (፪x)

እኔ ፡ አለሁኝ ፡ አለሁኝ ፡ አበዛለው ፡ ብዙ ፡ ምስጋና
ሰው ፡ ሆኛለሁ ፡ ጌታዬ ፡ ኢየሱሴ ፡ በሰራው ፡ ስራ
ከትላንቱ ፡ ከአስፈሪው ፡ ከጨለማው ፡ ከዚያ ፡ ግዛት
ያመለጠ ፡ የዳነ ፡ ለጌታዬ ፡ ይስገድለት
አምጡለታ ፡ አምጡለታ
ሲያንስበት ፡ ነው ፡ እልልታ ፡ ለዚህ ፡ ጌታ (፪x)

አዝ፦ የእኔን ፡ ነገር ፡ የእኔን ፡ ጉዳይ
የያዘልኝ ፡ ጌታ ፡ አለ ፡ ከሰማይ (፪x)

ማደሪያው ፡ ልግባና
ላምልከው ፡ አንስቼ ፡ በገና (፪x)

የዘላለም ፡ አባት ፡ የመዳኛ ፡ ደግሞም ፡ ካህኔ
እጅግ ፡ ብዙ ፡ ብዙ ፡ ነው ፡ አምለኬ ፡ የሆነው ፡ ለእኔ
ከአባቱ ፡ ቀኝ ፡ ሆኖ ፡ ስለእኔ ፡ እየማለደ
ዛሬም ፡ አለው ፡ በእቅፉ ፡ ጠላቴን ፡ እያዋረደ
አምጡለታ ፡ አምጡለታ
ሲያንስበት ፡ ነው ፡ እልልታ ፡ ለዚህ ፡ ጌታ (፪x)

አዝ፦ የእኔን ፡ ነገር ፡ የእኔን ፡ ጉዳይ
የያዘልኝ ፡ ጌታ ፡ አለ ፡ ከሰማይ (፪x)

ማደሪያው ፡ ልግባና
ላምልከው ፡ አንስቼ ፡ በገና (፬x)