Meskerem Getu/Eketelehalehu/Yenie Neger

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ


ዘማሪ መስከረም ጌቱ ርዕስ የእኔ ነገር አልበም እከተልሃለሁ

አዝ፦ የእኔን ነገር የእኔን ጉዳይ የያዘልኝ ጌታ አለ ከሰማይ (፪x)

ማደሪያው ልግባና ላምልከው አንስቼ በገና (፪x)

ከማማርረው አልሞላም ብዬ ስሙን ላወድስ ሀዘኔን ጥዬ ቢጐድልም እንኳን ወይኑ በለሱ በዚህ አይለካም ጌታ ነው እርሱ ጌታ ነው (፫x) ጌታ ላመስግነው ሳላይ ሁኔታ (፪x)

እኔ አለሁኝ አለሁኝ አበዛለሁ ብዙ ምስጋና ሰው ሆኛለሁ ጌታዬ ኢየሱሴ በሰራው ስራ ከትላንቱ ከአስፈሪው ከጨለማው ከዚያ ግዛት ያመለጠ የዳነ ለጌታዬ ይስገድለት አምጡለታ አምጡለታ ሲያንስበት ነው እልልታ ለዚህ ጌታ (፪x)

አዝ፦ የእኔን ነገር የእኔን ጉዳይ የያዘልኝ ጌታ አለ ከሰማይ (፪x)

ማደሪያው ልግባና ላምልከው አንስቼ በገና (፪x)

የዘላለም አባት የመዳኛ ደግሞም ካህኔ እጅግ ብዙ ብዙ ነው አምላኬ የሆነው ለእኔ ከአባቱ ቀኝ ሆኖ ስለእኔ እየማለደ ዛሬም አለሁ በእቅፉ ጠላቴን እያዋረደ አምጡለታ አምጡለታ ሲያንስበት ነው እልልታ ለዚህ ጌታ (፪x)

አዝ፦ የእኔን ነገር የእኔን ጉዳይ የያዘልኝ ጌታ አለ ከሰማይ (፪x)

ማደሪያው ልግባና ላምልከው አንስቼ በገና (፬x)