ጥበብን ፡ የሚሰጥ (Tebeben Yemiset) - መስከረም ፡ ጌቱ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ

የዝ መዝሙር

መስከረም ፡ ጌቱ
(Meskerem Getu)

Meskerem Getu 1.jpg


(1)

እከተልሃለሁ
(Eketelehalehu)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፭ (2012)
ቁጥር (Track):

(10)

ርዝመት (Len.): 4:21
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የመስከረም ፡ ጌቱ ፡ አልበሞች
(Albums by Meskerem Getu)

ጥበብን ፡ የሚሰጥ ፡ ጥበበኛ
የሕይወት ፡ ውኃ ፡ ወንዝ ፡ የእኔ ፡ መገኛ
እግዚአብሔር ፡ እርሱ ፡ የእኔ ፡ ነው
ኧረ/እስቲ ፡ ማነው ፡ ከእኔ ፡ ሚለየው (፪x)

ልጅ ፡ ቢወለድ ፡ ከባለጠጋ
ይካፈላል ፡ ከአባቱ ፡ ጋር
ሃብቱ ፡ ሁሉም ፡ ቅርሱ ፡ የእርሱ ፡ ነው
ግን ፡ የሚያልፍ ፡ ጊዜያዊ ፡ ነው

የእኔስ ፡ አባት ፡ ከሁሉ ፡ የላቀ
ሁሉን ፡ ገዢ ፡ በዓለም ፡ የታወቀ
እኮራለሁ ፡ ልጁ ፡ በመሆኔ
ኤልሻዳይ ፡ ነው ፡ አባቴ ፡ ለእኔ

ኃጢአት ፡ አልስራ ፡ እንጂ ፡ የማያከብረውን
ሌላ ፡ ምን ፡ ይኖራል ፡ እኔና ፡ እርሱን ፡ ሚለየን
በፀጋው ፡ በርትቼ ፡ እኖርለታለሁ
እንደ ፡ ሚያግዘኝ ፡ ጌታን ፡ አምነዋለሁ

አባ ፡ አባ ፡ ብዬ ፡ ስለው
አቤት ፡ ሚለኝ ፡ የቅርቤ ፡ ነው
ሚጠብቀኝ ፡ እንደ ፡ ዓይኑ ፡ ብሌን
ማን ፡ ሊወስደው ፡ ከእኔ ፡ ጌታዬን

የእኔስ ፡ አባት ፡ ከሁሉ ፡ የላቀ
ሁሉን ፡ ገዢ ፡ በዓለም ፡ የታወቀ
እኮራለሁ ፡ ልጁ ፡ በመሆኔ
ኤልሻዳይ ፡ ነው ፡ አባቴ ፡ ለእኔ

ኃጢአት ፡ አልስራ ፡ እንጂ ፡ የማያከብረውን
ሌላ ፡ ምን ፡ ይኖራል ፡ እኔና ፡ እርሱን ፡ ሚለየን
በፀጋው ፡ በርትቼ ፡ እኖርለታለሁ
እንደ ፡ ሚያግዘኝ ፡ ጌታን ፡ አምነዋለሁ