From WikiMezmur: Mezmur Lyrics
|
መስፍን ፡ ጉቱ ፡ እና ፡ ቴዎድሮስ ፡ ታደሰ (Mesfin & Teddy)
|
|
ልዩ ፡ እትም (Esp)
|
ሰላም ፡ ነው (Selam New)
|
ዓ.ም. (Year):
|
፳ ፻ ፫ (2010)
|
ቁጥር (Track):
|
፲ (10)
|
ርዝመት (Len.):
|
4:51
|
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች (Other Songs in the Album)
|
|
የመስፍን ፡ ጉቱ ፡ እና ፡ ቴዎድሮስ ፡ ታደሰ ፡ አልበሞች (Albums by Mesfin & Teddy)
|
|
አዝ፦ የሞት ፡ አዋጅ ፡ አይሰራም ፡ በሕይወቴ ፡ አይሆንም ፡ በሕይወቴ
ገልብጦታል ፡ ነገሩን ፡ አባቴ
የሞት ፡ አዋጅ ፡ አይሰራም ፡ በሕይወቴ ፡ አይሆንም ፡ በሕይወቴ
ገልብጦታል ፡ ኢየሱስ ፡ አባቴ
የሚውጠውን ፡ ፈልጐ ፡ እንደሚያገሳ ፡ አንበሳ (፪x)
ዙሪያ ፡ ዙሪያዬን ፡ ቢያንዣብብ ፡ ሰላሜን ፡ ደርሶ ፡ ሊነሳ (፪x)
መጣ ፡ ከሰማይ ፡ ወረደ ፡ ነደደ ፡ የአምላኬ ፡ ቁጣ (፪x)
በእሳት ፡ ቅጥሩ ፡ ቀጠረኝ ፡ ጠላት ፡ በበቀል ፡ ሳይወጣ (፪x)
ስልጣን ፡ የለውም ፡ በኔ ፡ ላይ
አለቃ ፡ አይሆንም ፡ የበላይ
እንዲያው ፡ አይደለም ፡ መጓደዴ
በመስቀል ፡ ሞት ፡ ነው ፡ መወለዴ (፬x)
አዝ፦ የሞት ፡ አዋጅ ፡ አይሰራም ፡ በሕይወቴ ፡ አይሆንም ፡ በሕይወቴ
ገልብጦታል ፡ ነገሩን ፡ አባቴ
የሞት ፡ አዋጅ ፡ አይሰራም ፡ በሕይወቴ ፡ አይሆንም ፡ በሕይወቴ
ገልብጦታል ፡ ኢየሱስ ፡ አባቴ
የስንቱን ፡ ጀግና ፡ ቤት ፡ ደፍሮ ፡ መቅሰፍቱን ፡ ይዞ ፡ ሲገባ (፪x)
አሳየኝ ፡ ገና ፡ ከሩቁ ፡ አጥፊውን ፡ ገዳዩን ፡ ሌባ (፪x)
ሸንጐ ፡ ሰብስቦ ፡ ሲመክር ፡ ታሪኬን ፡ መና ፡ ሊያደርገው (፪x)
ምልክት ፡ ሰጥቶ ፡ አስመለጠኝ ፡ እኔ ፡ የማመልከው ፡ እንዲህ ፡ ነው (፪x)
ስልጣን ፡ የለውም ፡ በኔ ፡ ላይ
አለቃ ፡ አይሆንም ፡ የበላይ
እንዲያው ፡ አይደለም ፡ መጓደዴ
በመስቀል ፡ ሞት ፡ ነው ፡ መወለዴ (፬x)
አዝ፦ የሞት ፡ አዋጅ ፡ አይሰራም ፡ በሕይወቴ ፡ (አይሰራም ፡ በሕይወቴ)
አይሆንም ፡ በሕይወቴ ፡ (አይሆንም ፡ በሕይወቴ)
ገልብጦታል ፡ ነገሩን ፡ አባቴ ፡ (ኢየሱስ ፡ አባቴ) (፪x)
|