Mesfin Gutu/Endihu Bewaza/Tesfayie

From WikiMezmur: Mezmur Lyrics
Jump to: navigation, search

ዘማሪ መስፍን ጉቱ አልበም እንዲሁ በዋዛ

ተስፋዬ ነህ አንተ ማረፊያዬ አንተ መታመንስ አንተ ኦ መመኪያ ነህ አንተ መመኪያዬ (፰x)


ተስፋዬ አንተው ነህ ንጉሤ አንተው ነህ አምላኬ አንተው ነህ ወዳጄ አንተው ነህ የሚሳንህ የለም ንገሥ የሚያቅትህ የለም ንገሥ የሚሳንህ የለም ንገሥ የሚያቅትህ የለም ንገሥ (፪x)


ከሸለቆ ወጣሁ ተራራ ላይ ቆምኩኝ ከረግረግ ውስጥ ወጣሁ እጄንም ተያዝኩኝ የጠላቴን አንገት ያስረገጠኝ ጌታ ይክበር ይንገሥልኝ ኢየሱስ የእኔ አለኝታ

ተስፋዬ ነህ አንተ ማረፊያዬ አንተ መታመንስ አንተ ኦ መመኪያ ነህ አንተ መመኪያዬ (፰x)


በበረሃ ጋሻ ለተጠማ እርካታ ስትሆን አየሁህ የእርሱ የእኔ ጌታ ጀርባህን ለደካማ ለበረታው ፊትህን ሰጥተህ አታደላም ሥምህ ብሩክ ይሁን (፭x)


ለታላቅነትህ እቀኛለሁ ለጌትነትህም እሰግዳለሁ (፫x) ኢየሱስ ጌታ ነህ (፫x)

የምስኪኑን ጥሪ ጩኸት ትሰማለህ በባዕድ ምድር ላይ አባት ትሆናለህ የተገፋን ማንሳት ማክበር ልማድህ ነው በሠማይ በምድር እንዳንተ ያለ ማነው (፬x)

ለታላቅነትህ እቀኛለሁ ለጌትነትህም እሰግዳለሁ ፫x) ኢየሱስ ጌታ ነህ (፫x)

ተስፋዬ ነህ አንተ ማረፊያዬ አንተ መታመንስ አንተ ኦ መመኪያ ነህ አንተ መመኪያዬ (፰x)