እግዚአብሔርን ፡ በመተማመን (Egziabhieren Bemetemamen) - መስፍን ፡ ጉቱ

From WikiMezmur: Mezmur Lyrics
Jump to: navigation, search
መስፍን ፡ ጉቱ
(Mesfin Gutu)

Mesfin Gutu Esp.png

ልዩ ፡ እትም
(Esp)

እንዲሁ ፡ በዋዛ
(Endihu Bewaza)

ዓ.ም. (Year): ፲ ፱ ፻ ፺ ፰ (2005)
ቁጥር (Track):

(7)

ርዝመት (Len.): 3:53
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የመስፍን ፡ ጉቱ ፡ አልበሞች
(Albums by Mesfin Gutu)

ኧረ ፡ ስንቱ ፡ በአንተ ፡ ታለፈ
የእኔ ፡ ጌታ ፡ በአንተ ፡ ታለፈ (፪x)

እግዚአብሔርን ፡ በመተማመን ፡ የሚጠባበቁ ፡ ሁሉ
ኃይላቸውን ፡ ያድሳሉ
እንደ ፡ ንስር ፡ በክንፍ ፡ ይወጣሉ

መስሎት ፡ ነበር ፡ ጠላቴ ፡ ደክሜ ፡ የምቀር
እግዚአብሔር ፡ ግን ፡ አበረታኝ ፡ ሆነልኝ ፡ ግርማ ፡ ሞገስ
ዛሬ ፡ ይኸው ፡ ዘምራለሁ ፡ ድካሜን ፡ ረስቻለሁ
ሥምህን ፡ አከብራለሁ ፡ ንገሥ ፡ እልሃለሁ (፪x)

አልደከምኩም ፡ አልታከትኩም ፡ ጌታ ፡ ሆኖኝ ፡ ኃይሌ
ዘለዓለም ፡ አመልከዋለሁ ፡ ኢየሱስ ፡ ጌታዬ
በደስታ ፡ በዕልልታ ፡ በአክብሮት ፡ ደግሞም ፡ በሆታ
ሥምህን ፡ አከብራልሁ ፡ ንገሥ ፡ እልሃለሁ