ኢየሩሳሌም (Eyerusaliem) - መሠረተ ፡ ክርስቶስ ፡ መዘምራን

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
መሠረተ ፡ ክርስቶስ ፡ መዘምራን
(Meserete Kristos Choir)

Meserete Kristos Choir 7.jpg


(7)

የታመንኩትን ፡ አውቃለሁ
(Yetamenkuten Awqalehu)

ዓ.ም. (Year): ፲ ፱ ፻ ፺ ፯ (2004)
ቁጥር (Track):

፲ ፪ (12)

ርዝመት (Len.): 5:34
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የመሠረተ ፡ ክርስቶስ ፡ መዘምራን ፡ አልበሞች
(Albums by Meserete Kristos Choir)

አዝ፦ ኢየሩሳሌም ፡ ቅድስቲት ፡ ከተማ
የጐዳናሽ ፡ ውጥንቅጡ ፡ ቢበዛ ፡ እንኳን
ሳላይሽ ፡ አልቀርም ፡ በአምላክ ፡ ኃይል ፡ እርዳታ (፪x)

የናፈቀኝ ፡ ዜማ ፡ የቅዱስ ፡ ዝማሬ (፪x)
አልቀርም ፡ ሳልዘምር ፡ ከጻድቃን ፡ አብሬ
ከበጉ ፡ ዙፋን ፡ ሥር ፡ ሳልዞር ፡ በደስታ (፪x)
አልቀርም ፡ ሳላይሽ ፡ አንች ፡ ቅዱስ ፡ ቦታ

አዝ፦ ኢየሩሳሌም ፡ ቅድስቲት ፡ ከተማ
የጐዳናሽ ፡ ውጥንቅጡ ፡ ቢበዛ ፡ እንኳን
ሳላይሽ ፡ አልቀርም ፡ በአምላክ ፡ ኃይል ፡ እርዳታ (፪x)

ማቋረጫው ፡ መንገድ ፡ ሊጠልፈኝ ፡ ቢነሳ (፪x)
ሳላየው ፡ አልቀርም ፡ የይሁድን ፡ አንበሳ
ብቻዬን ፡ ብቀርም ፡ መንገደኛው ፡ ሸሽቶ (፪x)
ሳልዘምር ፡ አልቀርም ፡ ኢየሱሴ ፡ መጥቶ

አዝ፦ ኢየሩሳሌም ፡ ቅድስቲት ፡ ከተማ
የጐዳናሽ ፡ ውጥንቅጡ ፡ ቢበዛ ፡ እንኳን
ሳላይሽ ፡ አልቀርም ፡ በአምላክ ፡ ኃይል ፡ እርዳታ (፪x)

የመናይ ፡ ተራራ ፡ መቧጠጥ ፡ ቢያቅተኝ (፪x)
የበረሃው ፡ ጉዞ ፡ ውኃ ፡ ጥም ፡ ቢጐዳኝ
የሚያረካው ፡ ጌታ ፡ ሲመታ ፡ ከሰማይ (፪x)
ይረዳኛል ፡ በርግጥ ፡ ያቺን ፡ ቦታ ፡ እንዳይ

አዝ፦ ኢየሩሳሌም ፡ ቅድስቲት ፡ ከተማ
የጐዳናሽ ፡ ውጥንቅጡ ፡ ቢበዛ ፡ እንኳን
ሳላይሽ ፡ አልቀርም ፡ በአምላክ ፡ ኃይል ፡ እርዳታ (፪x)