From WikiMezmur: Mezmur Lyrics
አዝ፦ ተነሥቷል (፪x) ፡ የመቃብር ፡ ደጃፍ ፡ ተከፍቷል
ድንጋዩ ፡ በሩቅ ፡ ተንከባሏል
ከፈኑ ፡ ብቻ ፡ ነው ፡ አስክሬኑ ፡ የታል?
በእውነትም ፡ ኢየሱስ ፡ ድል ፡ ነሥቷል (፪x)
ኢየሱስ ፡ ማሸነፉን ፡ ይስማ ፡ ኢየሩሳሌም
ይውጣ ፡ ምሥራቹ ፡ ከዓለም ፡ እስከዓለም
ይስማኝ ፡ ጠላትም ፡ መርዶውን ፡ አልቅሶ
ጌታ ፡ እንደው ፡ ተነስቷል ፡ አይሞት ፡ ተመልሶ
አዝ፦ ተነሥቷል (፪x) ፡ የመቃብር ፡ ደጃፍ ፡ ተከፍቷል
ድንጋዩ ፡ በሩቅ ፡ ተንከባሏል
ከፈኑ ፡ ብቻ ፡ ነው ፡ አስክሬኑ ፡ የታል?
በእውነትም ፡ ኢየሱስ ፡ ድል ፡ ነሥቷል
ይወገድ ፡ ድንጋዩ ፡ ጠባቂውም ፡ ይምጣ
ኢየሱስን ፡ ካቃተው ፡ ጌታ ፡ መውጫ ፡ ካጣ
የትኛው ፡ ጠባቂ ፡ ነው ፡ የከለከለው
ጌታ ፡ መቃብሩን ፡ ሲፈነቃቅለው
አዝ፦ ተነሥቷል (፪x) ፡ የመቃብር ፡ ደጃፍ ፡ ተከፍቷል
ድንጋዩ ፡ በሩቅ ፡ ተንከባሏል
ከፈኑ ፡ ብቻ ፡ ነው ፡ አስክሬኑ ፡ የታል?
በዕውነትም ፡ ኢየሱስ ፡ ድል ፡ ነሥስቷል
ይነገር ፡ ለዓለም ፡ ምስራች ፡ ይሰማ
ሞትን ፡ አሸንፏል ፡ ጀግናው ፡ ኢየሱስማ
ይህ ፡ ሐሰት ፡ አይደለም ፡ ዘለዓለም ፡ እውነት ፡ ነው
ይታይ ፡ የጌታችን ፡ መቃብር ፡ ባዶ ፡ ነው
አዝ፦ ተነሥቷል (፪x) ፡ የመቃብር ፡ ደጃፍ ፡ ተከፍቷል
ድንጋዩ ፡ በሩቅ ፡ ተንከባሏል
ከፈኑ ፡ ብቻ ፡ ነው ፡ አስክሬኑ ፡ የታል?
በእውነትም ፡ ኢየሱስ ፡ ድል ፡ ነሥቷል
ይሄ ፡ ነው ፡ እንግዲህ ፡ የጐልጐታው ፡ ሚስጥር
ወንጌላችን ፡ ኢየሱስ ፡ ከሙታንም ፡ በኩር
ሙትን ፡ አናመልክም ፡ መቃብር ፡ የዋጠ
ያሸነፈን ፡ እንጂ ፡ ሞትን ፡ ድል ፡ የነሳ
አዝ፦ ተነሥቷል (፪x) ፡ የመቃብር ፡ ደጃፍ ፡ ተከፍቷል
ድንጋዩ ፡ በሩቅ ፡ ተንከባሏል
ከፈኑ ፡ ብቻ ፡ ነው ፡ አስክሬኑ ፡ የታል?
በእውነትም ፡ ኢየሱስ ፡ ድል ፡ ነሥቷል
|