ጌታ ፡ ክበር ፡ ለዘለዓለም (Gieta Keber Lezelalem) - መሠረተ ፡ ክርስቶስ ፡ መዘምራን

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
መሠረተ ፡ ክርስቶስ ፡ መዘምራን
(Meserete Kristos Choir)

Meserete Kristos Choir 4.jpg


(4)

ጌታ ፡ ክበር ፡ ለዘለዓለም
(Gieta Keber Lezelalem)

ቁጥር (Track):

(2)

ርዝመት (Len.): 4:20
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የመሠረተ ፡ ክርስቶስ ፡ መዘምራን ፡ አልበሞች
(Albums by Meserete Kristos Choir)

የሱስ ንገሥ ለዘላለም

እንዳንተ ያለ የለም እንዳን ያለ (2)

 

    እስራኤል ተጨንቆ በግብፅ ባርነት

ጩኸቱን የሰማህ ከሰማይ ሰማያት

      ማንም በማይቀርበው ብርሃን የምትኖረው

      ክብር የሚገባው እግዚአብሔር ላንተ ነው

 

    በቤትልሔም ረሃብ ኑሃሚን ተሰዳ

      በልጆቿ መሞት አዝና ብትጎዳ

      ከጎኗ አቁመህ በሩት ያፅናናሃት

      እንዳንተ ያለ ማነው የደካማ ጉልበት

 

    በምስጋና ፊትህ ዛሬም እንቀርባለን

      ውለታህን ቆጥረን ያደረክልንን

      ዝማሬ ዘወትር ባፋችን ነውና

      ቅኔና ውዳሴ ይገባሃል ምስጋና

 

    የአጋንንትን ሥራ በስምህ አፍርሰህ

      የሰዎችን ኃጢአት በደምህ ደምስሰህ

      ዛሬም አትለወጥ አይሽሩህ ዘመናት

 

      ቃልህን ታፀናለህ በድንቅ በታምራት