From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
አዝ፦ ፍቅሩ ፡ የማያቋርጥ ፡ ጅረት ፡ ነው
አጥንትን ፡ ዘልቆ ፡ የሚሰማ
ልዩ ፡ ጣዕም ፡ የሞላው
የብርታት ፡ ቅኔ ፡ የሚያሰማ (፪x)
ፍቅርን ፡ ሳስባት ፡ ጌታ ፡ ኢየሱስን ፡ አልማለሁ
መላ ፡ አካላቴን ፡ አየዋለሁ
ፍቅሩ ፡ ሆን ፡ በውስጥ ፡ እረዳለሁ
የፍቅር ፡ ትርጉም ፡ እንደ ፡ ኢየሱስ ፡ የለም
አዝ፦ ፍቅሩ ፡ የማያቋርጥ ፡ ጅረት ፡ ነው
አጥንትን ፡ ዘልቆ ፡ የሚሰማ
ልዩ ፡ ጣዕም ፡ የሞላው
የብርታት ፡ ቅኔ ፡ የሚያሰማ (፪x)
ነፍስን ፡ ከመስጠት ፡ የበለጠ ፡ ነገር ፡ የለም
ይህችን ፡ ያህል ፡ ናት ፡ ፍቅር
ርህራሄ ፡ የሆነች ፡ ለዚህ ፡ ዓለም
ፍቅርን ፡ ለማየት ፡ ኢየሱስን ፡ መመልከት
አዝ፦ ፍቅሩ ፡ የማያቋርጥ ፡ ጅረት ፡ ነው
አጥንትን ፡ ዘልቆ ፡ የሚሰማ
ልዩ ፡ ጣዕም ፡ የሞላው
የብርታት ፡ ቅኔ ፡ የሚያሰማ (፪x)
ከወደደን ፡ ልብ ፡ ወስጥ ፡ ያለች ፡ ፍቅር ፡ መፈፀሚቱ
የገለፀልን ፡ በሞቱ
ያልተለወጠች ፡ በመስዋዕቱ
ፍቅርን ፡ ለመቅመስ ፡ በኢየሱስ ፡ መታደስ
አዝ፦ ፍቅሩ ፡ የማያቋርጥ ፡ ጅረት ፡ ነው
አጥንትን ፡ ዘልቆ ፡ የሚሰማ
ልዩ ፡ ጣዕም ፡ የሞላው
የብርታት ፡ ቅኔ ፡ የሚያሰማ (፪x)
|