ድል ፡ በድል (Del Bedel) - መሠረተ ፡ ክርስቶስ ፡ መዘምራን

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
Broom.png ይህ ፡ ጽሑፍ ፡ ገና ፡ አልተረጋገጠም ። እርማቶች ፡ ሊያስፈልጉት ፡ ይችላል ። ከቻሉ ፡ እርስዎ ፡ ያሻሽሉት
መሠረተ ፡ ክርስቶስ ፡ መዘምራን
(Meserete Kristos Choir)

Meserete Kristos Choir 1.jpg


(1)

እንዴት ፡ ድንቅ ፡ አምላክ ፡ ነው
(Endiet Denq Amlak New)

ቁጥር (Track):

፲ ፫ (13)

ርዝመት (Len.): 2:37
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የመሠረተ ፡ ክርስቶስ ፡ መዘምራን ፡ አልበሞች
(Albums by Meserete Kristos Choir)

አዝድል ፡ በድል ፡ ጐዳና (፪x)
ክርስቲያን ፡ አሸነፈ ፡ እየሱስ ፡ አለውና (፪x)

ያን ድቅድቅ ፡ ጨለማ ፡ የሞትን ፡ ሸለቆ
ታገለው ፡ ክርስቲያን ፡ የእምነት ፡ ትጥቁን ፡ ታጥቆ
አሻፈረኝ ፡ ብሎ ፡ ለእርሱ ፡ ላይረታ
በድል ፡ ጥሎት ፡ ወጣ ፡ በጌታው ፡ መከታ

አዝድል ፡ በድል ፡ ጐዳና (፪x)
ክርስቲያን አሸነፈ ፡ እየሱስ ፡ አለውና (፪x)

የጢሻን ፡ ጨለማ ፡ ብርሃን ፡ ወጣበት
ክርስቲያን ፡ በእምነት ፡ ሰይፍ ፡ አንዴ ፡ ቢዘምትበት
የማጥመጃ ፡ ሜዳ ፡ በደም ፡ አጥለቅልቆ
ሕያው ፡ ዘር ፡ ዘራበት ፡ እንዲበቅል ፡ አውቆ

አዝድል ፡ በድል ፡ ጐዳና (፪x)
ክርስቲያን አሸነፈ ፡ እየሱስ ፡ አለውና (፪x)

ጋሻ ፡ ጦሩን ፡ መንፈስ ፡ ፍላጻው ፡ እምነቱ
ማን ፡ ሊቋቋመው ፡ ነው ፡ ያንን ፡ ክንደ ፡ ብርቱ
ሊያጠምዱት ፡ ቢያስቀሩት ፡ አጥብቀው ፡ ቢጥሩም
ከአምላኩ ፡ ደም ፡ ቅጥር ፡ አልነቀለም ፡ እግሩን

አዝድል ፡ በድል ፡ ጐዳና (፪x
ክርስቲያን፡አሸነፈ ፡ እየሱስ ፡ አለውና (፪x)