የእግዚአብሔር ፡ ስራ (Yegziabhier Sera) - አዲስ ፡ አበባ ፡ መሠረተ ፡ ክርስቶስ ፡ መዘምራን

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
አዲስ ፡ አበባ ፡ መሠረተ ፡ ክርስቶስ ፡ መዘምራን
(Meserete Kristos Choir)

Meserete Kristos Choir 2.jpg


(2)

አሜን ፡ በሉ ፡ ስገዱለት
(Amien Belu Segedulet)

ቁጥር (Track):

፲ ፬ (14)

ርዝመት (Len.): 4:15
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የአዲስ ፡ አበባ ፡ መሠረተ ፡ ክርስቶስ ፡ መዘምራን ፡ አልበሞች
(Albums by Meserete Kristos Choir)

ድቅድቅ ጨለማውን ዘመን አልፈን ዛሬ ብርሃን አየን
ተመስገን ጌታ እግዚአብሔር በምድር በሰማይ ተከበር

አዝ፦ ተመስገን እስከዚህ ሰዓት ያደረስከን
ጌታ እግዚአብሔር ሆይ እኛ ማን ነን
መስዋዕት እንሰዋ ተንበርክከን ተመስገን (3)

ከመከራው ሸክም ብዛት ጎብጠን ባለፉት ዓመታት
ቀና ብለን እንድንራመድ ላበቃን ጌታ እንስገድ

አዝ፦ ተመስገን እስከዚህ ሰዓት ያደረስከን
ጌታ እግዚአብሔር ሆይ እኛ ማን ነን
መስዋዕት እንሰዋ ተንበርክከን ተመስገን (3)

ሐብታችንን ተቀምተን ከቤት ከሃገራችን ወጥተን
ስቅስቅ ብለን አልቅሰናል ይህን አይተህ እረድተኸናል

አዝ፦ ተመስገን እስከዚህ ሰዓት ያደረስከን
ጌታ እግዚአብሔር ሆይ እኛ ማን ነን
መስዋዕት እንሰዋ ተንበርክከን ተመስገን (3)

ሰዎች ተዘባበቱብን የዓለም ጉድፍ አደረጉን
ዛሬ ይኸው እንደገና አቁሞናል ለምስጋና

አዝ፦ ተመስገን እስከዚህ ሰዓት ያደረስከን
ጌታ እግዚአብሔር ሆይ እኛ ማን ነን
መስዋዕት እንሰዋ ተንበርክከን ተመስገን (3)

በደመና እስክትመለስ የዓለም ስደት ልንታገስ
ለዚህ ተጠርተናልና ጌታ ኢየሱስ ሆይ ቶሎ ና

አዝ፦ ተመስገን እስከዚህ ሰዓት ያደረስከን
ጌታ እግዚአብሔር ሆይ እኛ ማን ነን
መስዋዕት እንሰዋ ተንበርክከን ተመስገን (3)