ምንም ፡ ነገር ፡ የለንም (Menem Neger Yelenem) - አዲስ ፡ አበባ ፡ መሠረተ ፡ ክርስቶስ ፡ መዘምራን

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
አዲስ ፡ አበባ ፡ መሠረተ ፡ ክርስቶስ ፡ መዘምራን
(Meserete Kristos Choir)

Meserete Kristos Choir 2.jpg


(2)

አሜን ፡ በሉ ፡ ስገዱለት
(Amien Belu Segedulet)

ቁጥር (Track):

(9)

ርዝመት (Len.): 4:08
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የአዲስ ፡ አበባ ፡ መሠረተ ፡ ክርስቶስ ፡ መዘምራን ፡ አልበሞች
(Albums by Meserete Kristos Choir)

ምንም ነገር የለንም የኛ ነው የምንለው
ከአምላክ ያልተሰጠን ከላይ ያላገኘነው
ሁሉም የጌታችን ነው የቱን እኛ አተረፍን
ክብርና ሞገሳችን የሱስ ነው ፀጋን ያለበሰን

አዝ፦ አሜን በሉ ስለስጦታው አመስግኑት ስለውለታው
ሁለንተናችን የሱስ አብዝቶ ሰጠን ሁሉን (2)

የኛ እጃችን ባዶ ነው ጌታ ግን ይሞላናል
የኛ ለኛ የሆነው መኖሪያችን ምንድነው
ሁሉን በሱ አገኘን ባዶ ሸክላዎች ሳለን
ክብርና ሞገሳችን የሱስ ነው ፀጋን ያለበሰን

አዝ፦ አሜን በሉ ስለስጦታው አመስግኑት ስለውለታው
ሁለንተናችን የሱስ አብዝቶ ሰጠን ሁሉን (2)

የቱ ነው የእኛ ሃብት ውሃ አየር ፀሐይ ናት
ወይ እንቁ ወርቅ ከምድር ሊያሰመካን የሚደፍር
ይህ አለኝ የምንለው ለዚህ ዓለም የሰጠነው
ሁሉን በጌታ የሱስ አገኘን ፀጋን ባለበሰን

አዝ፦ አሜን በሉ ስለስጦታው አመስግኑት ስለውለታው
ሁለንተናችን የሱስ አብዝቶ ሰጠን ሁሉን (2)

ክብር ሃሌሉያ በሉ ጌታ ሰጥቶናል ሁሉን
እርሱን የሚያህል ምስጋና ይገባዋልና
ምንም ነገር ሳይኖረን ክቡር ሰው ያደረገን
ይክበር ይመስገን የሱስ ጌታችን ፀጋን ያለበሰን