የተሰዋህ (Yetesewah) - መሠረት ፡ ፅጌ ፡ እና ፡ እንዳልካቸው ፡ ኪዳነወልድ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
መሠረት ፡ ፅጌ ፡ እና ፡ እንዳልካቸው ፡ ኪዳነወልድ
(Meseret Tsegie and Endalkachew Kidanewold)

Meseret Tsegie and Endalkachew Kidanewold 1.jpg


(1)

የአዲስ ፡ ኪዳን ፡ በግ
(Yeadis Kidan Beg)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፪ (2010)
ቁጥር (Track):

(6)

ርዝመት (Len.): 5:06
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የመሠረት ፡ ፅጌ ፡ እና ፡ እንዳልካቸው ፡ ኪዳነወልድ ፡ አልበሞች
(Albums by Meseret Tsegie and Endalkachew Kidanewold)

አዝ፦ የተሰዋህ ፡ የእግዚአብሔር ፡ በግ
የሞትክልኝ ፡ አምላኬ ፡ ሆይ
ጭንቀት ፡ ጣርህ ፡ ለነፍሴ ፡ ይታይ (፪x)

ሃዘን ፡ ውጦኝ ፡ ሳለሁ ፡ ተጨንቄ
በድቅድቅ ፡ ጨለማ ፡ ውስጥ ፡ ወድቄ
ሳላስበው ፡ ድንገት ፡ ኢየሱስ ፡ ጠርቶኝ
የሕይወትን ፡ ውኃ ፡ አፈሰሰልኝ

አዝ፦ የተሰዋህ ፡ የእግዚአብሔር ፡ በግ
የሞትክልኝ ፡ አምላኬ ፡ ሆይ
ጭንቀት ፡ ጣርህ ፡ ለነፍሴ ፡ ይታይ (፪x)

የኀጢአት ፡ ሸክም ፡ እጅግ ፡ ጀብዶብኝ
ምንም ፡ አጥቼ ፡ የሚረዳኝ
ኢየሱሴ ፡ ድንገት ፡ ደርሶልኝ
ከድካሜ ፡ ሁሉ ፡ አሳረፈኝ

አዝ፦ የተሰዋህ ፡ የእግዚአብሔር ፡ በግ
የሞትክልኝ ፡ አምላኬ ፡ ሆይ
ጭንቀት ፡ ጣርህ ፡ ለነፍሴ ፡ ይታይ (፪x)

በሰይጣን ፡ ሰንሰለት ፡ ታስሬ
ወደገሃነም ፡ እሳት ፡ ሳመራ
ኢየሱሴ ፡ ለእኔ ፡ ዋስ ፡ ሆኖ
አወጣኝ ፡ ከዚያ ፡ መከራ

አዝ፦ የተሰዋህ ፡ የእግዚአብሔር ፡ በግ
የሞትክልኝ ፡ አምላኬ ፡ ሆይ
ጭንቀት ፡ ጣርህ ፡ ለነፍሴ ፡ ይታይ (፪x)

ተስፋ ፡ አልነበረኝም ፡ ከቶ
ከሲኦል ፡ ውስጥም ፡ ለመውጣቴ
በመስቀል ፡ ለእኔ ፡ ሞቶ ፡ አዳነኝ
ያየዋሁ ፡ ቸሩ ፡ አባቴ

አዝ፦ የተሰዋህ ፡ የእግዚአብሔር ፡ በግ
የሞትክልኝ ፡ አምላኬ ፡ ሆይ
ጭንቀት ፡ ጣርህ ፡ ለነፍሴ ፡ ይታይ (፪x)