መላኩ ማርቆስ (Melaku Markos)

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ



ብዬዋለሁ የኔ ጌታ ስለሆነልኝ መከታ ታሪክ ሰርቶ በህይወቴ አስደነቀኝ መድሀኒቴ

ምንም ሳይቸግረው ለኔ ሲል ተጎዳ ሲመቱት ሲገርፉት አርገው እንደ ባዳ የእየሱሴ ቁስል ለእኔ ፈውስ ሆኖልኝ ነፃ አውጥቶኛል ከፍ ይበልልኝ

ብዬዋለሁ የኔ ጌታ ስለሆነልኝ መከታ
 ታሪክ ሰርቶ በህይወቴ አስደነቀኝ መድሀኒቴ 

ከሞት አመለጥኩኝ በርሱ ተደግፌ(2) በህይወት አለሁኝ ከስቃይ አርፌ (2) ከዚያ ከጨለማ አወጣኝ መንጥቆ (2) ወዶ አከበረኝ ለኔ ሲል ተንቆ(2።

የማይከዳ የቅርብ ኋደኛ የሚራራ ወዳጅ ነው እርሱ
ጠርቶ መንገድ ላይ ጥሎ ለማይሸሽ ለሚጎበኘን በመንፈሱ
   ክብር ይሁን ለንጉሡ4×

እዳዬን ሊከፍል መስቀል ተሸክሞ ምራቅ እየተፉ ሲስቁበት ቆሞው በኔ ፈንታ ሞቶ ህይወቱን ሰጠኝ በዘላለም ፍቅሩ እኔን ወደደኝ

የማይከዳ የቅርብ ኋደኛ የሚራራ ወዳጅ ነው እርሱ
ጠርቶ መንገድ ላይ ጥሎ ለማይሸሽ ለሚጎበኘን በመንፈሱ
   ክብር ይሁን ለንጉሡ4×