እግዚአብሔርን ፡ ለሚወዱ (Egziabhieren Lemiwedu) - መቅደስ ፡ አዳሙ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
መቅደስ ፡ አዳሙ
(Mekdes Adamu)

Mekdes Adamu 2.jpg


(2)

ይነገርለት
(Yenegerelet)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፭ (2013)
ቁጥር (Track):

(6)

ርዝመት (Len.): 4:28
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የመቅደስ ፡ አዳሙ ፡ አልበሞች
(Albums by Mekdes Adamu)

አዝ፦ እግዚአብሔርን ፡ ለሚወዱት
እንዳሳቡ ፡ ደግሞ ፡ ለተጠሩ
ነገር ፡ ሁሉ ፡ ለበጐ
እንዲደረግ ፡ እናውቃለን (፪x) [1]

እግዚአብሔርን ፡ ለሚወዱት
እንዳሳቡም ፡ ለተጠሩ ፡ አሄ
ነገር ፡ ሁሉ ፡ ለበጐ ፡ ነው (፪x)

በዚጌውም ፡ አለጊዜው
ሊከብርብን ፡ የሚገባው ፡ እግዚአብሔር ፡ ነው
በዚጌውም ፡ አለጊዜው
ሊነግስብን ፡ የሚገባው ፡ ኢየሱሴ ፡ ነው

ለሁሉም ፡ ጊዜ ፡ አለው
ለሁሉም ፡ ነገር
ለሁሉም ፡ ቀን ፡ አለው
ለሁሉም (ለሁሉም ፡ ቀን ፡ አለው) (፪x)

አዝ፦ እግዚአብሔርን ፡ ለሚወዱት
እንዳሳቡ ፡ ደግሞ ፡ ለተጠሩ
ነገር ፡ ሁሉ ፡ ለበጐ
እንዲደረግ ፡ እናውቃለን (፪x) [1]

ነገሬን ፡ ሁሉ ፡ በዚጌው ፡ ውብ ፡ አድርጐ ፡ ሰራ
ከተሰራልኝ ፡ ነገር ፡ ለእኔስ ፡ የእኔ ፡ ጌታ (፪x)

ለሁሉም ፡ ጊዜ ፡ አለው
ለሁሉም ፡ ነገር
ለሁሉም ፡ ቀን ፡ አለው
ለሁሉም (ለሁሉም ፡ ቀን ፡ አለው/ነገር) (፪x)

እግዚአብሔር ፡ ይክብር ፡ እንጂ ፡ በሕይወቴ
ሌላው ፡ ሌላው ፡ ይሆናል ፡ አለው ፡ ጊዜው
ጌታ ፡ ኢየሱስ ፡ ይንገሥ ፡ እንጂ ፡ በሕይወቴ
ሌላው ፡ ሌላው ፡ ይሆናል ፡ አለው ፡ ጊዜው

አዝ፦ እግዚአብሔርን ፡ ለሚወዱት
እንዳሳቡ ፡ ደግሞ ፡ ለተጠሩ
ነገር ፡ ሁሉ ፡ ለበጐ
እንዲደረግ ፡ እናውቃለን (፪x) [1]

  1. 1.0 1.1 1.2 ሮሜ ፰:፳፰ (Romans 8:28)