ምሥጋናዬ (Mesganayie) - መካሻው ፡ ካሳ ፡ እና ፡ ፀባዖት ፡ ዕንግዳ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
መካሻው ፡ ካሳ ፡ እና ፡ ፀባዖት ፡ ዕንግዳ
(Mekashaw Kassa and Tsebaot Engeda)

Lyrics.jpg


(1)

ዘመን ፡ መጣልኝ
(Zemen Metalegn)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፬ (2011)
ቁጥር (Track):

(5)

ርዝመት (Len.): 5:02
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የመካሻው ፡ ካሳ ፡ እና ፡ ፀባዖት ፡ ዕንግዳ ፡ አልበሞች
(Albums by Mekashaw Kassa and Tsebaot Engeda)

አምላኬ ፡ የምሥጋናን ፡ መስዋዕት ፡ ለአንተ ፡ እሰዋለሁ
አምላኬ ፡ ሰልፉን ፡ ለአንተ ፡ ትቼ ፡ እኔ ፡ እዘምራለሁ (፪x)

አይጓደልብህ ፡ ምሥጋናዬ ፣ አይጓደልብህ ፡ አምልኮዬ(፪x)

በሰልፉ ፡ መሃል ፡ ቆሜ ፡ እዘምራለሁ (፪x)
ሃዘን ፡ ለቅሶዬን ፡ ትቼ ፡ እዘምራለሁ (፪x)
እዘምራለሁ (፬x)

በጭካኔ ፡ በትር ፡ በብዙ ፡ ቆሳስለው
ጳውሎስና ፡ ሲላስ ፡ እስር ፡ ቤት ፡ ተጥለው
ጸጥታው ፡ ይሰፍናል ፡ ወትሩም ፡ ሲሆን ፡ ሌሊት
ያኔ ፡ ግን ፡ ይሰማል ፡ ቁስለኛው ፡ ሲያቃስት

ይጠበቅ ፡ ነበር ፡ ማቃሰታቸው
ግን ፡ ተቀየረ ፡ ሌሊት ፡ ድምጻቸው
ሁኔታን ፡ ትተው ፡ ሲያመሰግኑ
የጌታ ፡ ኢየሱስ ፡ ታየ ፡ ማዳኑ

ዘምር ፡ ዘምር ፡ ይለኛል ፡ ኢየሱስን ፡ ሳስበው
አመስግነው ፡ ይለኛል ፡ ኢየሱስን ፡ ሳስበው (፪x)

ምሥጋናዬ ፡ ይጨምራል ፡ ገና
አምልኮዬ ፡ ይጨምራል ፡ ገና
ዝማሬዬ ፡ ይጨምራል ፡ ገና (፪x)

ንጉሥ ፡ እዮሳፍጥ ፡ ጠላቶች ፡ ከበውት
ንግስናውን ፡ ሊሽሩ ፡ እርስቱን ፡ ሊነጥቁት
የአባቶቹ ፡ አምላክ ፡ ፊቱን ፡ ቢፈልገዉ
ሰልፍ ፡ የእኔ ፡ ነው ፡ ብሎ ፡ ልቡን ፡ አሳረፈዉ

ምሥጋናን ፡ ይዞ ፡ ወጣ ፡ አደባባይ
ድልን ፡ አገኘ ፡ በጠላቱ ፡ ላይ
የአምላክ ፡ ድብቅ ፡ ጦር ፡ ተንቀሳቀሰ
ጠላት ፡ እርስ ፡ በእርስ ፡ ተጨራረሰ

አላወራውም ፡ የጠላቴን ፡ ሰልፍ ፡ ሃይለኛ ፡ ብዬ
አላወራውም ፡ አላስተጋባም ፡ ምሥጋናን ፡ ጥዬ

(ልማዴ ፡ ነው) ፡ በምሥጋና ፡ ላይ ፡ ለአንተ ፡ መጨመር
(ልማዴ ፡ ነው) ፡ ሁኔታን ፡ ትቶ ፡ ለአንተ ፡ መዘመር
(ባህሌ ፡ ነው) ፡ በምሥጋና ፡ ላይ ፡ ሌላ ፡ መጨመር
(ባህሌ ፡ ነው) ፡ ሁኔታን ፡ ትቶ ፡ ለአንተ ፡ መዘመር

ልማዴ ፡ ነው (፪x)
ባህሌ ፡ ነው (፪x)