በዋጋ (Bewaga) - ምህረት ፡ ኢተፋ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ምህረት ፡ ኢተፋ
(Meheret Etefa)

Meheret Etefa 4.jpg


(4)

ለየት ፡ ያለ ፡ ነው
(Leyet Yale New)

ዓ.ም. (Year): ፲ ፱ ፻ ፺ ፯ (2005)
ቁጥር (Track):

(4)

ርዝመት (Len.): 6:19
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የምህረት ፡ ኢተፋ ፡ አልበሞች
(Albums by Meheret Etefa)

በዋጋ ፡ ገዛኸኝ ፡ እንዳልጠፋ ፡ እንዳልሞት (፪x)
በዋጋ ፡ ገዛኸኝ ፡ እንዳልጠፋ ፡ እንዳልሞት (፪x)

ሃዘን ፡ መከራዬን ፡ ረሳሁ
በፊቱ ፡ ሞገስ ፡ አገኘሁ (፪x)
ክብር ፡ ለእግዚአብሔር
ለዚህ ፡ መብቃቴ ፡ እንዲህ ፡ መሆኔ
በእርሱ ፡ ብርታት ፡ ነው ፡ መች ፡ በእኔ
ክብር ፡ ይድረሰው ፡ መድህኔ
ክብር ፡ ለእግዚአብሔር (፯x)

አይደለም ፡ በእኔ ፡ በእኔ ፡ በኃይሌ
አይደለም ፡ በእኔ ፡ በእኔ (፪x)

ቅንነትህ (፫x)
አሰረኝ ፡ አሰረኝ ፡ የዋህነትህ

አንተ ፡ ቅንና ፡ ቸር ፡ የዋህ
ትህትናን ፡ ለሁሉ ፡ አስተማርክ
ከሃጥያት ፡ በቀር ፡ ስለሰው
በነገር ፡ ሁሉ ፡ ተፈተንክ ፡ አሃ
ተፈተንክ

ቅንነትህ (፫x)
አሰረኝ ፡ አሰረኝ ፡ የዋህነትህ

የግሌ ፡ ነህ ፡ የእራሴ
የብቻዬ ፡ ጌታዬ ፡ ለእኔ (፪x)

አይደለም ፡ በእኔ ፡ በእኔ ፡ በኃይሌ
አይደለም ፡ በእኔ ፡ በእኔ
አይደለም ፡ በእኔ

ቅንነትህ (፫x)
አሰረኝ ፡ አሰረኝ ፡ የዋህነትህ

ክብሩ (፫x)
ለእግዚአብሔር ፡ ለእርሱ ፡ ይሁንለት
ስራዬን ፡ ሰራልኝ ፡ አገኘሁ ፡ ነጻነት
ድንቅ ፡ ነው (፫x)
ሥራው ፡ አቤት ፡ ሲችልበት
ጠላትን ፡ ማንበርከክ ፡ አቤት ፡ ሲችልበት

እግዚአብሔር ፡ ቀደመ ፡ ኦሆሆሆ
ጠላቴን ፡ ገጠመ ፡ ኡሁሁ
ደገመ ፡ ደገመ ፡ ኦሆሆሆ
ፊቴ ፡ እየቀደመ ፡ ኡሁሁ (፪x)

ኤልሻዳይ ፡ ነው ፡ እርሱ ፡ ለማን ፡ ይበገራል
እግዚአብሔርን ፡ አይቶ ፡ ጠላቴም ፡ ፈርቶኛል (፪x)

ይሄ ፡ ነው (፭x)
ጌታ ፡ ድል ፡ አድራጊው (፪x)