From WikiMezmur: Mezmur Lyrics
አዝ፦ ባለግርማ ፡ ባለግርማ
ምሥጋናዬና ፡ አምልኮዬ ፡ ማደሪያህ ፡ ይግባ (፪x)
ባለሞገስ ፡ ባለሞገስ
ምሥጋናዬና ፡ አምልኮዬ ፡ ማደሪያህ ፡ ይድረስ (፪x)
ከአንተ ፡ በቀር ፡ አምላክ ፡ እኔ ፡ አላመልክም
ሌላ ፡ ሌላውን ፡ ልቤ ፡ አልፈቀደም
እሺ ፡ አላለኝም (፪x)
ባለግርማ ፡ ባለግርማ
ምሥጋናዬና ፡ አምልኮዬ ፡ ማደሪያህ ፡ ይግባ (፪x)
እንደ ፡ ሲድራቅ ፡ ሚሳቅ ፡ አብደናጐል [1]
ሰባት ፡ እጥፍ ፡ እሳቱ ፡ ቢነድም
ለቆመው ፡ ምስል ፡ አልዘምር ፡ አላደርገውም
ሰባት ፡ እጥፍ ፡ ይንደድ ፡ ምን ፡ ቸገረኝ
የማመልከው ፡ ይችላል ፡ ሊያድነኝ
በፈቃዴ ፡ ገባለሁ ፡ ይልቀቁኝ ፡ አያቃጥለኝም
አዝ፦ ባለግርማ ፡ ባለግርማ
ምሥጋናዬና ፡ አምልኮዬ ፡ ማደሪያህ ፡ ይግባ (፪x)
ባለሞገስ ፡ ባለሞገስ
ምሥጋናዬና ፡ አምልኮዬ ፡ ማደሪያህ ፡ ይድረስ (፪x)
ከአንተ ፡ በቀር ፡ አምላክ ፡ እኔ ፡ አላመልክም
ሌላ ፡ ሌላውን ፡ ልቤ ፡ አልፈቀደም
እሺ ፡ አላለኝም (፪x)
ባለግርማ ፡ ባለግርማ
ምሥጋናዬና ፡ አምልኮዬ ፡ ማደሪያህ ፡ ይግባ (፪x)
በዳንኤል ፡ እንደ ፡ እግዚአብሔር ፡ ሰው
በአንበሶች ፡ ጉድጓድ ፡ እንደ ፡ ተጣለው [2]
ግዑዙን ፡ አምላክ ፡ አላመልክም ፡ አላደርገውም
ይራቡ ፡ አንበሶቹ ፡ ምን ፡ ቸገረኝ
የማመልከው ፡ ከኔጋር ፡ ካለልኝ
ልሂድ ፡ ልግባ ፡ ይልቀቁኝ
አይችሉም ፡ ሊበሉኝ
አዝ፦ ባለግርማ ፡ ባለግርማ
ምሥጋናዬና ፡ አምልኮዬ ፡ ማደሪያህ ፡ ይግባ (፪x)
ባለሞገስ ፡ ባለሞገስ
ምሥጋናዬና ፡ አምልኮዬ ፡ ማደሪያህ ፡ ይድረስ (፪x)
ከአንተ ፡ በቀር ፡ አምላክ ፡ እኔ ፡ አላመልክም
ሌላ ፡ ሌላውን ፡ ልቤ ፡ አልፈቀደም
እሺ ፡ አላለኝም (፪x)
ባለግርማ ፡ ባለግርማ
ምሥጋናዬና ፡ አምልኮዬ ፡ ማደሪያህ ፡ ይግባ (፪x)
ለእርሱ ፡ ክብር ፡ አፌን ፡ እከፍታለሁ
ደስ ፡ እያለኝ ፡ እዘምርለታለሁ
ጐንበስ ፡ ቀና ፡ እያልኩኝ ፡ ለእርሱ ፡ እሰግድለታለሁ
እርሱ ፡ እኮ ፡ ነው ፡ በሕይወት ፡ ያኖረኝ
መከራዬን ፡ በሙሉ ፡ ያስረሳኝ
አልሰለችም ፡ እወድሰዋለሁ ፡ አመልከዋለሁ
አዝ፦ ባለግርማ ፡ ባለግርማ
ምሥጋናዬና ፡ አምልኮዬ ፡ ማደሪያህ ፡ ይግባ (፪x)
ባለሞገስ ፡ ባለሞገስ
ምሥጋናዬና ፡ አምልኮዬ ፡ ማደሪያህ ፡ ይድረስ (፪x)
ከአንተ ፡ በቀር ፡ አምላክ ፡ እኔ ፡ አላመልክም
ሌላ ፡ ሌላውን ፡ ልቤ ፡ አልፈቀደም
እሺ ፡ አላለኝም (፪x)
ባለግርማ ፡ ባለግርማ
ምሥጋናዬና ፡ አምልኮዬ ፡ ማደሪያህ ፡ ይግባ (፪x)
|
- ↑ ዳንኤል ፫ (Daniel 3)
- ↑ ዳንኤል ፮ (Daniel 6)