እንደ ፡ እኔማ ፡ ቢሆን (Endeniema Bihon) - ማሜ ፡ ወርቁ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ማሜ ፡ ወርቁ
(Mamay Worku)

Mamay Worku 1.jpg


(1)

ህልሜ
(Helmie)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፩ (2008)
ቁጥር (Track):

(3)

ርዝመት (Len.): 3:48
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የማሜ ፡ ወርቁ ፡ አልበሞች
(Albums by Mamay Worku)

እንደኔማ ፡ ቢሆን ፡ አልቆልኝ ፡ ነበረ
የበደሌ ፡ ብዛት ፡ እየተቆጠረ
ጌታዬ ፡ ግን ፡ አምላኬ ፡ ግን ፡ ዕዳዬን ፡ አስቀረ (፪x)

በዘለዓለም ፡ ሥሙ ፡ ቃልኪዳን ፡ ገባልኝ
አንቺ ፡ ልጅ ፡ በሕይወት ፡ ትኖሪያለሽ ፡ አለኝ
ጌታዬ ፡ ነው ፡ አዳኜ ፡ ነው ፡ እኔ ፡ እወደዋለሁ (፪x)

የኃጥያቴ ፡ ቀንበር ፡ ከብዶ ፡ እያስጨነቀኝ
ከሰው ፡ ሁሉ ፡ መሃል ፡ ነጥሎ ፡ እያስቀረኝ
ጌታዬ ፡ ግን ፡ አምላኬ ፡ ግን ፡ ፈልጐ ፡ አገኘኝ (፪x)

ያደረኩትን ፡ ሁሉ ፡ የልቤን ፡ ነገረኝ
ኃጥያቴን ፡ ሻረና ፡ ከሰው ፡ ቀላቀለኝ
አምላኬ ፡ ነው ፡ ጌታዬ ፡ ነው ፡ እኔ ፡ አመልከዋለሁ (፪x)

ዳግም ፡ ላልጠማ ፡ ቀንበር ፡ ላይጫነኝ
ከጨለማው ፡ ሰፈር ፡ ጠርቶ ፡ አወጣኝ
ጌታዬ ፡ ነው ፡ አምላኬ ፡ ነው ፡ እኔ ፡ አመልከዋለሁ (፪x)

ዝም ፡ በይ ፡ አትበሉኝ ፡ እኔ ፡ ዝም ፡ አልልም
የተረደገልኝ ፡ ዝም ፡ አያሰኘኝም
ኢየሱስ ፡ ነው ፡ እርሱ ፡ እኮ ፡ ነው ፡ ለእኔ ፡ የደረሰው
ጌታዬ ፡ ነው ፡ አምላኬ ፡ ነው ፡ እገዛለታለሁ