የቀደስካቸው (Yeqedeskachew) - ለዓለም ፡ ጥላሁን

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ለዓለም ፡ ጥላሁን
(Lealem Tilahun)

Lealem Tilahun 3.jpg


(3)

የናርዶስ ፡ ሽቶዬ
(Yenardos Shetoyie)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፮ (2014)
ቁጥር (Track):

(9)

ርዝመት (Len.): 5:26
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የለዓለም ፡ ጥላሁን ፡ አልበሞች
(Albums by Lealem Tilahun)

አዝየቀደስካቸው ፡ እጆቼን ፡ አንስቼ
ማምለክ ፡ ስጀምር ፡ ዓይኖቼን ፡ ወደላይ ፡ አቅንቼ (፪x)
ህዋሳቶቼ ፡ አካላቶቼ
አንተን ፡ ይሉኛል ፡ አጥንቶቼ
ህዋሳቶቼ ፡ አካላቶቼ
አንተን ፡ ይሉኛል ፡ አጥንቶቼ

ለሰው ፡ ልጅ ፡ ልማድነቱ
ክብርና ፡ ሞገስ ፡ በሕይወቱ
ለስብዕናውም ፡ ትርጉም
ከአንተ ፡ ውጭ ፡ አልተገኘም
ከአንተ ፡ ሌላ ፡ የለም ፡ የለም

አማራጭ ፡ የሌለህ ፡ ምርጫዬ
የሕይወቴ ፡ ገነት ፡ ተድላዬ
ያለ ፡ አንዳች ፡ ቅንጣት ፡ ቅሬታ
ፈቅጄ ፡ የማመልክህ ፡ በደስታ
እድል ፡ ፈንታዬ ፡ የእኔ ፡ ጌታ

አዝየቀደስካቸው ፡ እጆቼን ፡ አንስቼ
ማምለክ ፡ ስጀምር ፡ ዓይኖቼን ፡ ወደላይ ፡ አቅንቼ (፪x)
ህዋሳቶቼ ፡ አካላቶቼ
አንተን ፡ ይሉኛል ፡ አጥንቶቼ
ህዋሳቶቼ ፡ አካላቶቼ
አንተን ፡ ይሉኛል ፡ አጥንቶቼ

አጥንት ፡ ከአጥንት ፡ ሳይዋደድ
ሳልሰራ ፡ በእናቴ ፡ ሆድ
ቀኖቼን ፡ ጽፈህ ፡ በመጽሐፍ
እንደ ፡ ፈቃድህ ፡ እንደ ፡ ሀሳብህ
አራመድከኝ ፡ በትንቢት ፡ ቃልህ

አጋጣሚ ፡ አይደል ፡ ዎይ ፡ በድንገት
የሆንኩትን ፡ ሁሉ ፡ የሆንኩት
የሕይወቴን ፡ አቅጣጫ ፡ ቀያሪ
ፈላጭ ፡ ቆራጭ ፡ ሆኖ
አንተ ፡ ነህ ፡ የልቤ ፡ መርማሬ

አዝየቀደስካቸው ፡ እጆቼን ፡ አንስቼ
ማምለክ ፡ ስጀምር ፡ ዓይኖቼን ፡ ወደላይ ፡ አቅንቼ (፪x)
ህዋሳቶቼ ፡ አካላቶቼ
አንተን ፡ ይሉኛል ፡ አጥንቶቼ
ህዋሳቶቼ ፡ አካላቶቼ
አንተን ፡ ይሉኛል ፡ አጥንቶቼ