ፍፁም ፡ እንከን ፡ የለው ፡ ውበትህ (Fetsum Enken Yelew Webeteh) - ለዓለም ፡ ጥላሁን

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ለዓለም ፡ ጥላሁን
(Lealem Tilahun)

Lealem Tilahun 3.jpg


(3)

የናርዶስ ፡ ሽቶዬ
(Yenardos Shetoyie)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፮ (2014)
ቁጥር (Track):

(5)

ርዝመት (Len.): 5:43
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የለዓለም ፡ ጥላሁን ፡ አልበሞች
(Albums by Lealem Tilahun)

አዝ፦ እኔማ ፡ ቢሆንልኝማ
በክብርህ ፡ ውስጥ ፡ አድሬ
በህልውናህ ፡ ኖሬ
ያን ፡ መልካሙን ፡ ፈትህን
ታይቶ ፡ የማይጠገበውን
ካገኘሁ ፡ ያኔ ፡ ኖርኩኝ/ረካሁ ፡ እላለሁ (፪x)

ፍፁም ፡ እንከን ፡ የሌው ፡ ውብትህ
ደናግሎች ፡ አይተው ፡ ወደድዱህ (፪x)
ሳበኝ ፡ እሮጣለሁ ፡ ከኋልህ
ሳይህ ፡ ውዬ ፡ ባድር ፡ አልጠግብህ
ሳይህ ፡ ውዬ ፡ ባድር ፡ አልጠግብህ (፪x)

አልጠግብህ (፮x)
አልጠግብህ ፡ ጌታ ፡ አልጠግብህ

የዕድሜ ፡ ልክ ፡ ፍስሃ ፡ በቀኝህ
የሚያበራ ፡ ፀዳል ፡ ስላለህ (፪x)
ፃድቅ ፡ በብርሃንህ ፡ ይራመዳል
ከህልውናህ ፡ ውጭ ፡ የት ፡ ይኬዳል (፪x)

አዝ፦ እኔማ ፡ ቢሆንልኝማ
በክብርህ ፡ ውስጥ ፡ አድሬ
በህልውናህ ፡ ኖሬ
ያን ፡ መልካሙን ፡ ፈትህን
ታይቶ ፡ የማይጠገበውን
ካገኘሁ ፡ ያኔ ፡ ኖርኩኝ/ረካሁ ፡ እላለሁ (፪x)

የተትረፈረፈ ፡ ነው ፡ ፅዋዬ
ከአምላክ ፡ ፊት ፡ ሆኖልኝ ፡ ገበታዬ (፪x)
የንጉሥ ፡ ማዕረግ ፡ ለምዳለች ፡ ነፍሴ
ተጣብቃልኝ ፡ በኢየሱሴ (፪x)

በኢየሱሴ (፰x)