ዙፋንህ ፡ የዘላለም ፡ ነው (Zufanih Yezelalem New) - ለዓለም ፡ ጥላሁን

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ለዓለም ፡ ጥላሁን
(Lealem Tilahun)

Lealem Tilahun 1.jpg


(1)

ኃይልንም ፡ የሚያስታጥቀኝ
(Hailenem Yemiyastateqegn)

ዓ.ም. (Year): ፲ ፱ ፻ ፺ ፪ (2000)
ቁጥር (Track):

(8)


ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የለዓለም ፡ ጥላሁን ፡ አልበሞች
(Albums by Lealem Tilahun)

 
አመታቶችህ ፡ ከቶ ፡ አያልቁም
የዘመንህ ፡ ቁጥር ፡ አይመረመርም
አልፋ ፡ ኦሜጋ ፡ ፊተኛ ፡ ኋለኛ
የእግዚአብሔር ፡ ልጅ ፡ ንጉስ ፡ ነህ ፡ ለእኛ
 
አዝ:- ዙፋንህ ፡ የዘላለም ፡ ነው
መንግሥትህ ፡ ማንም ፡ አይሽረው
አንተ ፡ ግን ፡ አንተው ፡ ነህ ፡ ዘላለም
ኢየሱስ ፡ የሚመስልህ ፡ የለም (፪x)
 
ስልጣን ፡ የአንተ ፡ ነው ፡ መንግስት ፡ የአንተ ፡ ነው
አምላክና ፡ አባት ፡ አዳኝ ፡ የሆንከው
የሲኦልን ፡ ቁልፍ ፡ በእጅህ ፡ ይዘሃል
ጻድቅ ፡ ፈራጅ ፡ ነህ ፡ ክብር ፡ ይገባሃል
 
አዝ:- ዙፋንህ ፡ የዘላለም ፡ ነው
መንግሥትህ ፡ ማንም ፡ አይሽረው
አንተ ፡ ግን ፡ አንተው ፡ ነህ ፡ ዘላለም
ኢየሱስ ፡ የሚመስልህ ፡ የለም (፪x)

ከጥንት ፡ ጀምሮ ፡ ምድርን ፡ መሰረትክ
በእጆች ፡ ሥራ ፡ ሰማይን ፡ ሰራህ
የፍጥረት ፡ ገዢ ፡ አምላክ ፡ አንተ ፡ ነህ
ሁሉም ፡ ያልፋሉ ፡ አንተ ፡ ግን ፡ ያው ፡ ነው
 
አዝ:-ዙፋንህ ፡ የዘላለም ፡ ነው
መንግሥትህ ፡ ማንም ፡ አይሽረው
አንተ ፡ ግን ፡ አንተው ፡ ነህ ፡ ዘላለም
ኢየሱስ ፡ የሚመስልህ ፡ የለም (፪x)
 
ከስሞች ፡ በላይ ፡ ታላቅ ፡ ስም ፡ ይዘህ
በአባትህ ፡ ቀኝ ፡ በክብር ፡ ያለህ
የሁሉ ፡ ጌታ ፡ የሁሉ ፡ ንጉስ
የእኛም ፡ መድሃኒት ፡ አንተ ፡ ነህ ፡ ኢየሱስ
 
አዝ:- ዙፋንህ ፡ የዘላለም ፡ ነው
መንግሥትህ ፡ ማንም ፡ አይሽረው
አንተ ፡ ግን ፡ አንተው ፡ ነህ ፡ ዘላለም
ኢየሱስ ፡ የሚመስልህ ፡ የለም (፪x)