Lealem Tilahun/Hailenem Yemiyastateqegn/Hailenem Yemiyastateqegn

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ


ለዓለም ፡ ጥላሁን (ዶ/ር)
(Lealem Tilahun, Dr)
Lyrics.jpg

(1)

ኃይልንም ፡ የሚያስታጥቀኝ (Hailenem Yemiyastateqegn)
ቁጥር (Track):

(2)

ዓ.ም. (Year): '


አዝ:-ሁሉን አርገህልኛል የቀረብኝ የለም
ሌላ የምልህ ባይኖረኝ እወድሃለሁኝ
ሌላ የምልህ ባይኖረኝ እወድሃለሁኝ

የሰማይን ጸጋ የምድርን በረከት
በሌላ አይደለም ባንተ ነው ያገኘሁት
ጽድቅና ሰላምን የመንፈስን ደስታ
አጎኛጽፈኸኛል የሰራዊት ጌታ

አዝ:-ሁሉን አርገህልኛል የቀረብኝ የለም
ሌላ የምልህ ባይኖረኝ እወድሃለሁኝ
ሌላ የምልህ ባይኖረኝ እወድሃለሁኝ

ምን ያጠያይቃል መልካምነትህ
ለኔስ ጌታ ኢየሱስ በረከቴ ነህ
መወደድ ሲያንስህ ነው መቼ ይበዛብሃል
እንኳን እኔነቴ ዘሬ ይገዛልሃል

እየዋለ እያደር ታምራትህ በዛ
የነገስታት ንጉስ የጌቶችም ጌታ /2/

ምን እንልሃለን ማዳንህን እያየን
ከምስጋና በላይ ምስጋና እንሰዋለን
ምን እንለሃለን ምህረትህን እያየን
ከክብርም በላይ ክብርን እንሰጣለን

መልካም ማድረግን ማይታክትህ
አቤት እግዚአብሔር ቸርነትህ
ትላንት ያረከው ሳይበቃህ
ዛሬም ደገምከኝ አብዝተህ /2/

በክብር ላይ ሌላ ክብር በክብር ላይ አሃሃ
ቆርጬያለሁ ለመጨመር ከዚያም በላይ
አንደበቴን በምስጋና እየከፈትኩ ኦሆ
ለድል ጌታ የደል ዜማ አመጣለሁ

ተራሮችንም ትክክል
አደረክና እግዚአብሄር አሃሃ
የናሱን ደጆች ሰባብረህ
እኔን ለክብርህ አበቃኸኝ

በክብር ላይ ሌላ ክብር በክብር ላይ አሃሃ
ቆርጬያለሁ ለመጨመር ከዚያም በላይ
አንደበቴን በምስጋና እየከፈትኩ ኦሆ
ለድል ጌታ የደል ዜማ አመጣለሁ

አምላኬ መታመኛዬ ነህ ጌታዬ
ንጉሴ መደገፊያዬ ነህ አንባዬ /2/

አዝ:-ሃይልንም የሚያስታጥቀኝ
ቅጥሩንም የሚያዘልለኝ
እግሮቼን የሚያበረታ
የሚያቆመኝ በከፍታ

ዛረ ታሪኬ ተለውጥዋል
ጠላት እያየ ይቃጠላል አሃሃ
ጌታ ሰጥቶኛል መሻቴን
ዘይት ቀብቶ እራሴን

{{#customtitle: ኃይልንም ፡ የሚያስታጥቀኝ (Hailenem Yemiyastateqegn)}}