እየዋለ ፡ እያደር (Eyewale Eyader) - ለዓለም ፡ ጥላሁን

From WikiMezmur: Mezmur Lyrics
Jump to: navigation, search
ለዓለም ፡ ጥላሁን
(Lealem Tilahun)

Lealem Tilahun 1.jpg


(1)

ኃይልንም ፡ የሚያስታጥቀኝ
(Hailenem Yemiyastateqegn)

ዓ.ም. (Year): ፲ ፱ ፻ ፺ ፪ (2000)
ቁጥር (Track):

(1)


ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የለዓለም ፡ ጥላሁን ፡ አልበሞች
(Albums by Lealem Tilahun)

 
አዝ:- ሁሉን ፡ አድርገህልኛል ፡ የቀረብኝም ፡ የለም
ሌላ ፡ ምልህ ፡ ባይኖረኝ ፡ እወድሃለሁ ፡ እኔም
ሌላ ፡ ምልህ ፡ ባይኖረኝ ፡ እወድሃለሁ ፡ እኔም (፪x)

የሰማይን ፡ ፀጋ ፡ የምድርን ፡ በረከት
በሌላ ፡ እኮ ፡ አይደለም ፡ ባንተ ፡ ነው ፡ ያገኘሁት
ጽድቅና ፡ ሰላምን ፡ የመንፈስን ፡ ደስታ
አጎናጽፈኅኛል ፡ የሰራዊት ፡ ጌታ (፪x)
 
አዝ:- ሁሉን ፡ አድርገህልኛል ፡ የቀረብኝም ፡ የለም
ሌላ ፡ ምልህ ፡ ባይኖረኝ ፡ እወድሃለሁ ፡ እኔም
ሌላ ፡ ምልህ ፡ ባይኖረኝ ፡ እወድሃለሁ ፡ እኔም (፪x)
 
ምን ፡ ያጠያይቃል ፡ መልካምነትህ
ለኔስ ፡ ጌታ ፡ ኢየሱስ ፡ በረከቴ ፡ ነህ
መወደድ ፡ ስይንስህ ፡ ነው ፡ መች ፡ ይበዛብሃል
እንኳን ፡ እኔነቴ ፡ ዘሬ ፡ የገዛልሃል
 
እየዋለ ፡ እያደር ፡ ታምራትህ ፡ በዛ
የነገስታት ፡ ንጉስ ፡ የጌቶቹ ፡ ጌታ (፪x)
 
ምን ፡ እንልሃለን ፡ ማዳንህን ፡ እያየን
በምስጋና ፡ በላይ ፡ ምስጋናን ፡ እንሰዋለን
ምን ፡ እንልሃለን ፡ ምሕረትህን ፡ እያየን
በክብርም ፡ በላይ ፡ ክብርን ፡ እንሰጣለን
 
መልካምን ፡ ማድረግ ፡ ማይታክትህ
አቤት ፡ እግዚአብሔር ፡ ቸርነትህ ፡ አሃሃ
ትላንት ፡ ያረከው ፡ ሳይበቃህ
ዛሬም ፡ ደገምከኝ ፡ አብዝተህ (፪x)
 
በክብር ፡ ላይ ፡ ሌላ ፡ ክብር ፡ በክብር ፡ ላይ ፡ አሃ
ቆርጫለሁ ፡ ለመጨመር ፡ ከዚያም ፡ በላይ
አንደበቴን ፡ በምስጋና ፡ እየከፈትኩ ፡ ኦሆ
ለድል ፡ ጌታ ፡ የድል ፡ ዜማን ፡ አመጣለሁ
 
እየዋለ ፡ እያደር ፡ ታምራትህ ፡ በዛ
የነገስታት ፡ ንጉስ ፡ የጌቶቹ ፡ ጌታ (፪x)
 
ምን ፡ እንልሃለን ፡ ማዳንህን ፡ እያየን
በምስጋና ፡ በላይ ፡ ምስጋናን ፡ እንሰዋለን
ምን ፡ እንልሃለን ፡ ምሕረትህን ፡ እያየን
በክብርም ፡ በላይ ፡ ክብርን ፡ እንሰጣለን

ተራሮችንም ፡ ትክክል ፡ አደረክና ፡ እግዚአብሔር ፡ አሃ
የነሃሱን ፡ ደጆች ፡ ሰባብረህ ፡ እኔን ፡ ለክብር ፡ አበቃህ (፪x)
 
በክብር ፡ ላይ ፡ ሌላ ፡ ክብር ፡ በክብር ፡ ላይ ፡ አሃ
ቆርጫለሁ ፡ ለመጨመር ፡ ከዚያም ፡ በላይ
አንደበቴን ፡ በምስጋና ፡ እየከፈትኩ ፡ ኦሆ
ለድል ፡ ጌታ ፡ የድል ፡ ዜማን ፡ አመጣለሁ
 
አምላኬ ፡ መታመኛዬ ፡ ነው ፡ ጌታዬ
ንጉሴ ፡ መደገፊያዬ ፡ ነው ፡ አምባዬ (፪x)