እያየሁ (Eyayehu) - ቅድስት ፡ ካሳ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ቅድስት ፡ ካሳ
(Kidist Kassa)

Kidist Kassa 1.png


(1)

ተውድጃለሁ
(Tewedejalehu)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፰ (2008)
ቁጥር (Track):

(1)

ርዝመት (Len.): 4፡47
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የቅድስት ፡ ካሳ ፡ አልበሞች
(Albums by Kidist Kassa)

አዝ፦ የታመንኩትን ፡ አዉቀዋለሁ
ክንዱ ፡ ሲረዳኝ ፡ አይቻለሁ
ሰምቶ ፡ በእሳት ፡ የሚመልስ
ምዘምርለት ፡ ጌታ ፡ እየሱስ

እያየዉ ፡ በመቀሉ ፡ ስራ
እያየዉ ፡ ሁሉን ፡ እየጠራ
እያየዉ ፡ በጨለማ ፡ ላሉ
እያየዉ ፡ ብርሃን ፡ ሲበራ
ልቤ ፡ ተነሳ ፡ ለመዘመር ፡ ለእግዚሐብሄር
ልቤ ፡ ተነሳ ፡ ለመዘመር ፡ ለእግዚሐብሄር

አዝ፦ የታመንኩትን ፡ አዉቀዋለሁ
ክንዱ ፡ ሲረዳኝ ፡ አይቻለሁ
ሰምቶ ፡ በእሳት ፡ የሚመልስ
ምዘምርለት ፡ ጌታ ፡ እየሱስ

እያየዉ ፡ ባሕሩን ፡ ሲከፍል
እያየዉ ፡ ሕዝቡን ፡ ሲያሻግር
እያየዉ ፡ በምድረበዳ ፡ ላይ
እያየዉ ፡ ከለላ ፡ ሲሆን
ልቤ ፡ ተነሳ ፡ ለመዘመር ፡ ለእግዚሐብሄር
ልቤ ፡ ተነሳ ፡ ለመዘመር ፡ ለእግዚሐብሄር

አዝ፦ የታመንኩትን ፡ አዉቀዋለሁ
ክንዱ ፡ ሲረዳኝ ፡ አይቻለሁ
ሰምቶ ፡ በእሳት ፡ የሚመልስ
ምዘምርለት ፡ ጌታ ፡ እየሱስ

እያየዉ ፡ ደዌዉን ፡ ሲፈዉስ
እያየዉ ፡ እንባቸዉን ፡ ሲያብስ
እያየዉ ፡ እስራት ፡ ሲፈታ
እያየዉ ፡ ሲያመልኩ ፡ በደስታ
ልቤ ፡ ተነሳ ፡ ለመዘመር ፡ ለእግዚሐብሄር
ልቤ ፡ ተነሳ ፡ ለመዘመር ፡ ለእግዚሐብሄር

ብዙ ፡ ምስጋና ፡ ለጌታ
ብዙ ፡ ክብር ፡ ለጌታ
ብዙ ፡ እልልታ ፡ ለጌታ ፡ ለጌቶች ፡ ጌታ ለጌታ
ለጌታ….ለጌታ…..ለጌታ