Kefa Mideksa/Hulum Yesma/Hulum Yesma

From WikiMezmur: Mezmur Lyrics
Jump to: navigation, search


ዘማሪ ኬፋ ሚደቅሳ አልበም ሁሉም ይስማ

አዝ

አንተ እንደ ረዳኸኝ
አንተ እንዳነሳኸኝ

ሁሉ ይስማ ይወቅልኝ
ሁሉ ይስማ ያመስግንልኝ
ሁሉ ይስማ ይወቅልኝ
ሁሉ ይስማ ያመስግንልኝ (፪x)


ምደረ በዳውን አቋርጫለሁ
እጄን ይዘኸኝ ኢየሱስ በሕይወት ኖሪያለሁ
አልነደፈኝም እባቡ ጊንጡ
አቤት ኢየሱስ በአንተ ተረፍኩ ከስንቱ (፪x)
አቤት አባቴ በአንተ ተረፍኩ ከስንቱ


ሲጨላልም የማይነጋ ሲመስል
የቅርብ የሩቅ ገለል ገለል ሲል
በውድቅቱ ሌሊቱ መጣህና
በሰልፍ ቀን ራሴን ሸፈንክና
አዘመርከኝ (፫x)
እንዳዳንኩህ እንዳገዝኩህ መስክር አልከኝ
አባት ሆንከኝ ክብር ሆንከኝ ተሸከምከኝ
በደግ እጅህ እቅፍ አርገህ አነሳኸኝ


በምህረትህ ብዛት ቤት አግብተኸኛል አሃሃ (፪x)
ቤት አግብተኸኛል
በፊትህ ቃል ደስታ ለእኔ ሰጥተኸኛል አሃሃ (፪x)
ለእኔ ሰጥተኸኛል
ደግሜ ደግሜ የማመሰግንህ ምክኒያቴ ብዙ ነው አሃሃ (፪x)
ምክኒያቴ ብዙ ነው ከዛ ከጨካኙ ነፍሴን ከሚፈልግ
ከአውሬ አስጥለኸኝ ነው አሃሃ (፪x)
ከአውሬ አስጥለኸኝ ነው

አዝ


አንተ እንደ ረዳኸኝ
አንተ እንዳነሳኸኝ
ሁሉ ይስማ ይወቅልኝ
ሁሉ ይስማ ያመስግንልኝ
ሁሉ ይስማ ይወቅልኝ
ሁሉ ይስማ ያመስግንልኝ (፪x)