Kefa Mideksa/Hulum Yesma/Hulum Yesma

From WikiMezmur: Mezmur Lyrics
Jump to: navigation, search


ዘማሪ ኬፋ ሚደቅሳ አልበም ሁሉም ይስማ አዝ አንተ እንደ ረዳኸኝ አንተ እንዳነሳኸኝ ሁሉ ይስማ ይወቅልኝ ሁሉ ይስማ ያመስግንልኝ ሁሉ ይስማ ይወቅልኝ ሁሉ ይስማ ያመስግንልኝ (፪x)

ምደረ በዳውን አቋርጫለሁ እጄን ይዘኸኝ ኢየሱስ በሕይወት ኖሪያለሁ አልነደፈኝም እባቡ ጊንጡ አቤት ኢየሱስ በአንተ ተረፍኩ ከስንቱ (፪x) አቤት አባቴ በአንተ ተረፍኩ ከስንቱ

ሲጨላልም የማይነጋ ሲመስል የቅርብ የሩቅ ገለል ገለል ሲል በውድቅቱ ሌሊቱ መጣህና በሰልፍ ቀን ራሴን ሸፈንክና

አዘመርከኝ (፫x) እንዳዳንኩህ እንዳገዝኩህ መስክር አልከኝ አባት ሆንከኝ ክብር ሆንከኝ ተሸከምከኝ በደግ እጅህ እቅፍ አርገህ አነሳኸኝ

በምህረትህ ብዛት ቤት አግብተኸኛል አሃሃ (፪x) ቤት አግብተኸኛል በፊትህ ቃል ደስታ ለእኔ ሰጥተኸኛል አሃሃ (፪x) ለእኔ ሰጥተኸኛል ደግሜ ደግሜ የማመሰግንህ ምክኒያቴ ብዙ ነው አሃሃ (፪x) ምክኒያቴ ብዙ ነው ከዛ ከጨካኙ ነፍሴን ከሚፈልግ ከአውሬ አስጥለኸኝ ነው አሃሃ (፪x) ከአውሬ አስጥለኸኝ ነው

አዝ አንተ እንደ ረዳኸኝ አንተ እንዳነሳኸኝ ሁሉ ይስማ ይወቅልኝ ሁሉ ይስማ ያመስግንልኝ ሁሉ ይስማ ይወቅልኝ ሁሉ ይስማ ያመስግንልኝ (፪x)