ምክርህ ፡ ሲፀና (Mekereh Sitsena) - ኬፋ ፡ ሚደቅሳ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ኬፋ ፡ ሚደቅሳ
(Kefa Mideksa)

Kefa Mideksa 3.jpg


(3)

ሁሉ ፡ በእጁ ፡ ነው
(Hulu Beju New)

ዓ.ም. (Year): ፲ ፱ ፻ ፺ ፰ (2006)
ቁጥር (Track):

፲ ፫ (13)

ርዝመት (Len.): 4:42
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የኬፋ ፡ ሚደቅሳ ፡ አልበሞች
(Albums by Kefa Mideksa)

ምክርህ ፡ ሲሰራ ፡ አይቼ ፡ ተደስቻለሁ
ማይከለከል ፡ ሃሳብህ ፡ አውቄዋለሁ
ድንቅህን ፡ አይቼ ፡ ብገረም ፡ ቆምኩኝ ፡ ላመልክህ
በሰው ፡ ሁሉ ፡ ፊት ፡ ተገልጧል ፡ አደራረግህ

አዝ፦ ተባረክ ፡ ከዚህ ፡ ሌላ ፡ ምን ፡ እላለሁ
ጌታዬ ፡ አንተ ፡ ነህ ፡ አውቄያለሁ
ዘመኔን ፡ ከአንተ ፡ ጋር ፡ እንድኖር ፡ ጌታ
በቃልህ/በምክርህ ፡ ደገፍከኝ ፡ እንዳልረታ (፪x)

አንተን ፡ አምኜ ፡ ወደፊት ፡ እራመዳለሁ
ወሬ ፡ ሰምቼ ፡ ኋላዬን ፡ መቼ ፡ አያለሁ
ዘለዓለሜ ፡ በእጅህ ፡ ነው ፡ ልቤ ፡ እንዳይሰጋ
የምታመንህ ፡ ጌታዬ ፡ አለህ ፡ ከእኔ ፡ ጋር

አዝ፦ ተባረክ ፡ ከዚህ ፡ ሌላ ፡ ምን ፡ እላለሁ
ጌታዬ ፡ አንተ ፡ ነህ ፡ አውቄያለሁ
ዘመኔን ፡ ከአንተ ፡ ጋር ፡ እንድኖር ፡ ጌታ
በቃልህ/በምክርህ ፡ ደገፍከኝ ፡ እንዳልረታ (፪x)

የሰው ፡ ዓይን ፡ የለህ ፡ እንደሰው ፡ መቼ ፡ ታያለህ
ጆሮህስ ፡ እንደሰማቸው ፡ መች ፡ ትፈርዳለህ
መንገዱ ፡ ይሄ ፡ ነው ፡ ብሎ ፡ ሚመራህ ፡ የለም
በምክርህ ፡ ግሩም ፡ ትክክል ፡ ጻድቅ ፡ አምላክ ፡ ነህ

አዝ፦ ተባረክ ፡ ከዚህ ፡ ሌላ ፡ ምን ፡ እላለሁ
ጌታዬ ፡ አንተ ፡ ነህ ፡ አውቄያለሁ
ዘመኔን ፡ ከአንተ ፡ ጋር ፡ እንድኖር ፡ ጌታ
በቃልህ/በምክርህ ፡ ደገፍከኝ ፡ እንዳልረታ (፪x)

ለዘሪ ፡ ዘርን ፡ የምትሰጥ ፡ ፍሬ ፡ እንዲበላ
ከሕይወት ፡ እንዳይጐድል ፡ ሞቶ ፡ የኋላ ፡ ኋላ
ለእኔም ፡ ቃልህን ፡ ሰጥተኸኛል ፡ ምን ፡ አስባለሁ
ተስፋ ፡ ቢስ ፡ ሆኜ ፡ አልቀረሁም ፡ አከብርሃለሁ

አዝ፦ ተባረክ ፡ ከዚህ ፡ ሌላ ፡ ምን ፡ እላለሁ
ጌታዬ ፡ አንተ ፡ ነህ ፡ አውቄያለሁ
ዘመኔን ፡ ከአንተ ፡ ጋር ፡ እንድኖር ፡ ጌታ
በቃልህ/በምክርህ ፡ ደገፍከኝ ፡ እንዳልረታ (፪x)