ከማስበውና (Kemasebewena) - ኬፋ ፡ ሚደቅሳ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ኬፋ ፡ ሚደቅሳ
(Kefa Mideksa)

Kefa Mideksa 3.jpg


(3)

ሁሉ ፡ በእጁ ፡ ነው
(Hulu Beju New)

ዓ.ም. (Year): ፲ ፱ ፻ ፺ ፰ (2006)
ቁጥር (Track):

፲ ፪ (12)

ርዝመት (Len.): 4:56
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የኬፋ ፡ ሚደቅሳ ፡ አልበሞች
(Albums by Kefa Mideksa)

ያለእርሱ ፡ ፈቃድ ፡ የበላ ፡ ተድላን ፡ የቀመሰ ፡ ማነው
እስትንፋስ ፡ ያለው ፡ በሙሉ ፡ ሲመካ ፡ ሚያምረው ፡ በእርሱ ፡ ነው
ለሃጥን ፡ ለጻድቁ ፡ ሰው ፡ ፀሐይን ፡ እኩል ፡ ያወጣል
በግሌ ፡ ተገርሜርያለሁ ፡ ጌታ ፡ ከአይምሮዬ ፡ ያልፋል

አዝ፦ ከማስበውና ፡ ከምገምተው
በላይ ፡ ያደረገው ፡ እግዚአብሔር ፡ ነው (፪x)

የለመንኩትን ፡ ብቻ ፡ አይደለም ፡ ጨምሮ ፡ ሌላም ፡ ሰጥቶኛል
ያልጠበኩትን ፡ በረከት ፡ ፀጋውን ፡ ደርቦልኛል
ከእጆቹ ፡ የተቀበልኩት ፡ ስጦታው ፡ እንዴት ፡ መልካም ፡ ነው
ቅሬታ ፡ የለም ፡ በልቤ ፡ ያረገው ፡ ሁሉ ፡ መልካም ፡ ነው

አዝ፦ ከማስበውና ፡ ከምገምተው (በላይ)
በላይ ፡ ያደረገው ፡ እግዚአብሔር ፡ ነው (፪x)

የምህረት ፡ ደጁ ፡ አልተዘጋም
አምላኬ ፡ በዚህ ፡ አይታማም
እርሱ ፡ እኮ ፡ ባለፀጋ ፡ ነው
ለሚፈልጉት ፡ ቅርብ ፡ ነው (፪x)

አዝ፦ ከማስበውና ፡ ከምገምተው (በላይ)
በላይ ፡ ያደረገው ፡ እግዚአብሔር ፡ ነው (፪x)

ያለእርሱ ፡ ፈቃድ ፡ የበላ ፡ ተድላን ፡ የቀመሰ ፡ ማነው
እስትንፋስ ፡ ያለው ፡ በሙሉ ፡ ሲመካ ፡ ሚያምረው ፡ በእርሱ ፡ ነው
ለሃጥን ፡ ለጻድቁ ፡ ሰው ፡ ፀሐይን ፡ እኩል ፡ ያወጣል
በግሌ ፡ ተገርሜርያለሁ ፡ ጌታ ፡ ከአይምሮዬ ፡ ያልፋል

አዝ፦ ከማስበውና ፡ ከምገምተው (በላይ)
በላይ ፡ ያደረገው ፡ እግዚአብሔር ፡ ነው (፪x)