Kasahun Lema/Egziabhier Qen Alew/Eyesus Yehiwotie

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ

በእቅፍህ ፡ መሃል ፡ ስፍራን ፡ ሰጠኸኝ ፡ ተደላድዬ እፎይ ፡ ብያለሁ ፡ አንተን ፡ አግኝቼ ፡ ክበር ፡ ጌታዬ እንዳልታወክ ፡ በቀኜ ፡ አለህ ፡ ውስጤ ፡ መች ፡ ሰግቶ ልቤም ፡ ይጣራል ፡ ኢየሱስ ፡ እያለ ፡ በፍቅርህ ፡ ነዶ (፪x)

አዝ፦ (ኢየሱስ) ፡ የሕይወቴ ፡ ትርጉም ፡ (ኢየሱስ) ፡ የሆንክልኝ ፡ ፍቺ (፪x)
(ኢየሱስ) ፡ ክብርን ፡ አይቻለሁ ፡ (ኢየሱስ) ፡ እኔስ ፡ በአንተ ፡ እጅ (፪x)

ሁሉን ፡ ቻይ ፡ አምላክ ፡ ወረት ፡ የማታውቅ ፡ እሩህሩህ ፡ ጌታ ፍቅርህ ፡ ማረከኝ ፡ የአንተ ፡ እንድሆን ፡ ልቤም ፡ ተረታ ሌላ ፡ አይገዛንም ፡ ከአንተ ፡ በስተቀር ፡ በምድር ፡ ያለው ሁሉ ፡ የሞላህ ፡ ባለ ፡ ፀጋ ፡ አምላክ ፡ አንተን ፡ ይዣለሁ (፪x)

ክበርልኝ (፫x)
አላየሁም ፡ ከአንተ ፡ የሚበልጥብኝ
ንገስልኝ (፫x)
አልሰማሁም ፡ ከአንተ ፡ የሚበልጥብኝ

አላየሁም ፡ ከአንተ ፡ የምበልጥብኝ አልሰማሁም ፡ ከአንተ ፡ የምበልጥብኝ (፪x)

ስትሾም ፡ ስትሸልም ፡ (አቤት ፡ ስታውቅበት)
ደርሰህ ፡ ብርሃን ፡ (ስትሆን ፡ ቀን ፡ ለጨለመበት)

ስታውቅበት ፡ ማበጃጀት