From WikiMezmur: Mezmur Lyrics
|
ቃልኪዳን ፡ (ሊሊ) ፡ ጥላሁን (Kalkidan Tilahun)
|
|
፫ (3)
|
ይታየኛል ፡ ብዙ ፡ ነገር (Yetayegnal Bezu Neger)
|
ቁጥር (Track):
|
፭ (5)
|
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች (Other Songs in the Album)
|
|
የቃልኪዳን ፡ (ሊሊ) ፡ ጥላሁን ፡ አልበሞች (Albums by Kalkidan Tilahun)
|
|
ምህረቱ ፡ ገነነ ፡ በላዬ (፪x)
ባርኮቱ ፡ ገነነ ፡ በላዬ (፪x)
የበረከት ፡ አምላክ ፡ መባረክን ፡ ያውቃል
እጁ ፡ ያጠግባል ፣ እጁ ፡ ያጠግባል (፪x)
የበረከት ፡ አምላክ ፡ መባረክን ፡ ያውቃል
እጁ ፡ ያጠግባል ፡ እጁ ፡ ያጠግባል
እጁ ፡ ያጠግባል ፡ የእኔ ፡ ጌታ ፡ እጁ ፡ ያጠግባል
ምህረቱ ፡ ገነነ ፡ በላዬ (፪x)
ባርኮቱ ፡ ገነነ ፡ በላዬ (፪x)
በቃ ፡ በቃ ፡ ክረምት ፡ አለፈ
በጋው ፡ መጣ ፡ የመከራው ፡ ዘመን
ሁሉ ፡ ተረሳ ፡ የመከራው ፡ ዘመን ፡ ሁሉ ፡ ተረሳ
ከዓለት ፡ ንቃቃቱ ፡ ወጥቻለሁ ፡ የኢየሱሴን ፡ ማዳን
አወራለሁ ፡ የኢየሱሴን ፡ ማዳን ፡ አወራለሁ
ከዓለት ፡ ንቃቃቱ ፡ ወጥቻለሁ ፡ ድምጼን ፡ ለጌታዬ
አሰማለሁ ፡ ድምጼን ፡ ለጌታዬ ፡ አሰማለሁ
የበረከት ፡ አምላክ ፡ መባረክን ፡ ያውቃል
እጁ ፡ ያጠግባል ፣ እጁ ፡ ያጠግባል
የበረከት ፡ አምላክ ፡ መባረክን ፡ ያውቃል
እጁ ፡ ያጠግባል ፣ እጁ ፡ ያጠግባል ፡ የእኔ ፡ ጌታ
እጁ ፡ ያጠግባል ፣ እጁ ፡ ያጠግባል
ምድረ ፡ በዳውን ፡ ኤደን ፡ በረሃውንም ፡ ገነት
አድርገኸዋል ፣ አድርገኸዋል
ድስታና ፡ ተድላ ፡ ምሥጋናና ፡ ዝማሬ
ለእኔስ ፡ ሰጥተሃል ፣ ለእኔ ፡ ሰጥተሃል (፪x)
በጐ ፡ ስጦታ ፡ ፍፁም ፡ በረከት
አንተ/ከላይ ፡ ነህና ፡ የብርሃናት ፡ አባት (፪x)
አመልከዋለሁ ፡ አመልከዋለሁ (፫x)
ምህረቱ ፡ ገነነ ፡ በላዬ (፪x)
ባርኮቱ ፡ ገነነ ፡ በላዬ (፪x)
ምህረቱ ፡ ገነነ ፡ በላዬ (፪x)
ባርኮቱ ፡ ገነነ ፡ በላዬ (፪x)
|