ትንፋሽ ፡ እስከሚያጥረኝ (Tenfash Eskemiyatregn) - ቃልኪዳን ፡ ጥላሁን

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ቃልኪዳን ፡ ጥላሁን
(Kalkidan Tilahun)

Kalkidan Tilahun 5.jpg


(5)

ለእግዚአብሔር ፡ ቀላል ፡ ነው
(LeEgziabhier Qelal New)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፪ (2010)
ቁጥር (Track):

(6)

ርዝመት (Len.): 6:33
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የቃልኪዳን ፡ ጥላሁን ፡ አልበሞች
(Albums by Kalkidan Tilahun)

ትንፋሽ ፡ እስከሚያጥረኝ ፡ ቃላት ፡ እስከማጣ
ተደንቂያለሁኝ ፡ ወደ ፡ እኔ ፡ ስትመጣ (፪x)

ማይሆንን ፡ ነገር ፡ ይሆናል ፡ ብለህ
ማይቻለውን ፡ ይቻላል ፡ ብለህ
ይኸው ፡ አስደነከኝ ፡ እንዲህ ፡ አድርገህ (፪x)

አቤት ፡ አምላኬ ፡ አርገህልኛል
የልቤን ፡ ሃሳብ ፡ ሞልተህልኛል
አቤት ፡ ጌታዬ ፡ አርገህልኛል
የልቤን ፡ ሁሉ ፡ ሞልተህልኛል
የልቤን ፡ ሃሳብ ፡ ሞልተህልኛል
የልቤን ፡ ሁሉ ፡ ሞልተህልኛል

አንተ ፡ ተናጥቀህ ፡ ለእኔ ፡ ብለህ
አስደናቂ ፡ ነገር ፡ ይኸው ፡ አደረገ (፪x)

አቤት ፡ አምላኬ ፡ አርገህልኛል
የልቤን ፡ ሃሳብ ፡ ሞልተህልኛል
አቤት ፡ ጌታዬ ፡ አርገህልኛል
የልቤን ፡ ሁሉ ፡ ሞልተህልኛል
የልቤን ፡ ሃሳብ ፡ ሞልተህልኛል
የልቤን ፡ ሁሉ ፡ ሞልተህልኛል

ትንፋሽ ፡ እስከሚያጥረኝ ፡ ቃላት ፡ እስከማጣ
ተደንቂያለሁኝ ፡ ወደ ፡ እኔ ፡ ስትመጣ (፪x)

በእኔ ፡ ብልጠት ፡ በእኔ ፡ ጉብዝና
ኢሄ ፡ ሁሉ ፡ አልሆንምና
እከፍላለሁ ፡ አሃ ፡ ለአንተ ፡ ምሥጋና (፪x)

እከፍላለሁ ፡ አሃ ፡ ምሥጋናህን
እከፍላለሁ ፡ ኦሆ ፡ አምልኮህን
እከፍላለሁ ፡ አሃ ፡ ዝማሬህን
እከፍላለሁ ፡ ኦሆ ፡ ተመሥገንህን

ክፍል ፡ አደርጋለሁ ፡ በደስታ
ኢሄም ፡ ያንስበታል ፡ ለዚህ ፡ ጌታ (፪x)

እየበሉ ፡ እተጠጡ ፡ ዝም
ኢሄ ፡ ነገር ፡ እኔ ፡ አይገባኝም
እከፍላለሁ ፡ እኔስ ፡ በደስታ
ተመሥገኔ ፡ ይገባዋል ፡ ጌታ

እከፍላለሁ ፡ አሃ ፡ ምሥጋናህን
እከፍላለሁ ፡ ኦሆ ፡ አምልኮህን
እከፍላለሁ ፡ አሃ ፡ ዝማሬህን
እከፍላለሁ ፡ ኦሆ ፡ ተመሥገንህን

ክፍል ፡ አደርጋለሁ ፡ በደስታ
ኢሄም ፡ ያንስበታል ፡ ለዚህ ፡ ጌታ
ክፍል ፡ አደርጋለሁ ፡ እንደገና
ሌላም ፡ ሌላም ፡ ነገር ፡ ጭምርና

በእኔ ፡ ብልጠት ፡ በእኔ ፡ ጉብዝና
ኢሄ ፡ ሁሉ ፡ አልሆንምና
እከፍላለሁ ፡ አሃ ፡ ለአንተ ፡ ምሥጋና (፪x)

አቤት ፡ አምላኬ ፡ አርገህልኛል
የልቤን ፡ ሃሳብ ፡ ሞልተህልኛል
አቤት ፡ ጌታዬ ፡ አርገህልኛል
የልቤን ፡ ሁሉ ፡ ሞልተህልኛል
የልቤን ፡ ሃሳብ ፡ ሞልተህልኛል
የልቤን ፡ ሁሉ ፡ ሞልተህልኛል
(፪x)