From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
|
ቃልኪዳን ፡ ጥላሁን (Kalkidan Tilahun)
|
|
፩ (1)
|
አልበም (1)
|
ዓ.ም. (Year):
|
፲ ፱ ፻ ፺ ፯ (2004)
|
ቁጥር (Track):
|
፩ (1)
|
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች (Other Songs in the Album)
|
|
የቃልኪዳን ፡ ጥላሁን ፡ አልበሞች (Albums by Kalkidan Tilahun)
|
|
የማይሆነው ፡ ላይሆን ፡ የሚሆነው ፡ ላይቀር
ምንድነው ፡ መጨነቅ ፡ ምንድነው ፡ መሸበር
እግዚአብሔር ፡ እያለ ፡ ሁሉን ፡ የሚችለው
ነፍሴ ፡ ሆይ ፡ ማዘነሽ ፡ ከቶ ፡ ለምንድን ፡ ነው
አዝ፦ ነፍሴ ፡ አታስጨንቂኝ
እስቲ ፡ በእግዚአብሔር ፡ ታመኚ (፪x)
እስኪ ፡ ያለፍሽበትን ፡ ጐዳና
ኣንቺ ፡ መለስ ፡ ብልሽ ፡ እይና
ጌታ ፡ ከምን ፡ ከምን ፡ አዳንሽ
እንዴት ፡ እንዴት ፡ አርጐስ ፡ ታደገሽ (፪x)
አዝ፦ ነፍሴ ፡ አታስጨንቂኝ
እስቲ ፡ በእግዚአብሔር ፡ ታመኚ (፪x)
ጌታ ፡ ምህረቱን ፡ ዘጋ ፡ ወይ
ይሄ ፡ ስንፈናዬ ፡ አይደል ፡ ወይ
እርሱ ፡ ቢዘገየም ፡ ይመጣል
ሁሉን ፡ አዲስ ፡ አዲስ ፡ ያደርጋል
ፊትህን ፡ ወደኔ ፡ ከመለስክልኝ
አንተን ፡ ደስ ፡ ካለህ ፡ ካልተቆጣኸኝ (፪x)
ዓይኖችህ ፡ ካዩኝ ፡ ጆሮህን ፡ ከሰማኝ
ይሄ ፡ ይበቃኛል ፡ እረካለሁኝ (፪x)
አለኝ ፡ ይምለው
ተስፋ ፡ ማደርገው ፡ የምመካበት
መገኘትህ ፡ ብቻ ፡ ነው
ፊትህን ፡ ብቻ ፡ ነው
መገኘትህ ፡ ብቻ ፡ ነው
ፍቅርህን ፡ ብቻ ፡ ነው
አለኝ ፡ ይምለው
ተስፋ ፡ ማደርገው ፡ የምመካበት
ፍቅርህን ፡ ብቻ ፡ ነው (፪x)
ህልውናህ ፡ ብቻ ፡ ነው
መገኘትህ ፡ ብቻ ፡ ነው
|