የማይሆነው ፡ ላይሆን (Yemayhonew Layhon) - ቃልኪዳን ፡ ጥላሁን

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ቃልኪዳን ፡ ጥላሁን
(Kalkidan Tilahun)

Lyrics.jpg


(Volume)

አመሰግናለሁ
(Amesegenalehu)

ዓ.ም. (Year): ፲ ፱ ፻ ፺ ፯ (2004)
ቁጥር (Track):

(1)


ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የቃልኪዳን ፡ ጥላሁን ፡ አልበሞች
(Albums by Kalkidan Tilahun)

የማይሆነው ፡ ላይሆን ፡ የሚሆነው ፡ ላይቀር
ምንድነው ፡ መጨነቅ ፡ ምንድነው ፡ መሸበር
እግዚአብሔር ፡ እያለ ፡ ሁሉን ፡ የሚችለው
ነፍሴ ፡ ሆይ ፡ ማዘነሽ ፡ ከቶ ፡ ለምንድን ፡ ነው

አዝ፦ ነፍሴ ፡ አታስጨንቂኝ
እስቲ ፡ በእግዚአብሔር ፡ ታመኚ (፪x)

እስኪ ፡ ያለፍሽበትን ፡ ጐዳና
ኣንቺ ፡ መለስ ፡ ብልሽ ፡ እይና
ጌታ ፡ ከምን ፡ ከምን ፡ አዳንሽ
እንዴት ፡ እንዴት ፡ አርጐስ ፡ ታደገሽ (፪x)

አዝ፦ ነፍሴ ፡ አታስጨንቂኝ
እስቲ ፡ በእግዚአብሔር ፡ ታመኚ (፪x)

ጌታ ፡ ምህረቱን ፡ ዘጋ ፡ ወይ
ይሄ ፡ ስንፈናዬ ፡ አይደል ፡ ወይ
እርሱ ፡ ቢዘገየም ፡ ይመጣል
ሁሉን ፡ አዲስ ፡ አዲስ ፡ ያደርጋል

ፊትህን ፡ ወደኔ ፡ ከመለስክልኝ
አንተን ፡ ደስ ፡ ካለህ ፡ ካልተቆጣኸኝ (፪x)
ዓይኖችህ ፡ ካዩኝ ፡ ጆሮህን ፡ ከሰማኝ
ይሄ ፡ ይበቃኛል ፡ እረካለሁኝ (፪x)

አለኝ ፡ ይምለው
ተስፋ ፡ ማደርገው ፡ የምመካበት
መገኘትህ ፡ ብቻ ፡ ነው
ፊትህን ፡ ብቻ ፡ ነው
መገኘትህ ፡ ብቻ ፡ ነው
ፍቅርህን ፡ ብቻ ፡ ነው

አለኝ ፡ ይምለው
ተስፋ ፡ ማደርገው ፡ የምመካበት
ፍቅርህን ፡ ብቻ ፡ ነው (፪x)
ህልውናህ ፡ ብቻ ፡ ነው
መገኘትህ ፡ ብቻ ፡ ነው