From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
|
ቃልኪዳን ፡ ጥላሁን (Kalkidan Tilahun)
|
|
፩ (1)
|
አቤቱ ፡ ጉልበቴ ፡ ሆይ ፡ እወድሃለሁ (አቤቱ ፡ ጉልበቴ ፡ ሆይ ፡ እወድሃለሁ (Abietu Gulbetie Hoy Ewedihalehu) (Vol. 1))
|
ቁጥር (Track):
|
፲ (10)
|
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች (Other Songs in the Album)
|
|
የቃልኪዳን ፡ ጥላሁን ፡ አልበሞች (Albums by Kalkidan Tilahun)
|
|
አዝ፦ ማራናታ (፫x)
ቶሎ ፡ ና ፤ የኔ ፡ ጌታ ፤ የኔ ፡ ጌታ (፪x)
ቃልህን ፡ በመግለጥ፧ ፡ ዓለምን ፡ ሙላና
በድንቅ ፡ በተዓምር ፡ ተመላለስና
አንተን ፡ ተቀብለው ፡ ነፍሳት ፡ ይዳኑና
የኔ ፡ ጌታ ፡ ኢየሱስ ፡ እባክህ ፡ ቶሎ ፡ ና
አዝ፦ ማራናታ (፫x)
ቶሎ ፡ ና ፤ የኔ ፡ ጌታ ፤ የኔ ፡ ጌታ
እመጣለሁ ፡ ብለህ ፡ ቃል ፡ ገብተህልናል
ቃልህ ፡ እንዲፈጸም ፡ ልጆችህ ፡ ናፍቀናል
የታረደውን ፡ በግ ፡ ስለበደላችን
ልናይ ፡ እንወዳለን ፡ ሁላችን ፡ በዓይናችን
አዝ፦ ማራናታ (፫x)
ቶሎ ፡ ና ፤ የኔ ፡ ጌታ ፤ የኔ ፡ ጌታ
በዕንቁ ፡ በወርቅ ፡ አርጐ ፡ እግዚአብሔር ፡ የሰራት
ጥላቻ ፡ ተረስቶ ፡ ፍቅር ፡ የሞላባት
ለእኛ ፡ ለልጆቹ ፡ አምላክ ፡ ያዘጋጃት
ኢየሩሳሌምን ፡ መቼ ፡ ነው ፡ የማያት
አዝ፦ ማራናታ (፫x)
ቶሎ ፡ ና ፤ የኔ ፡ ጌታ ፤ የኔ ፡ ጌታ (፪x)
|