እፁብ ፡ ነህ ፡ አንተ (Etsub Neh Ante) - ቃልኪዳን ፡ ጥላሁን

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ

አዝ፦ እፁብ ፡ ነህ ፡ አንተ ፡ አንተ ፡ አትለወጥም
ግሩም ፡ ነህ ፡ አንተ ፡ ስራህም ፡ አያልቅም (፪x)

እግዚአብሔር ፡ አለ ፡ በማደሪያው
እግዚአብሔር ፡ አለ ፡ በዙፋኑ (፪x)

ሰማይ ፡ ዙፋንህ ፡ ነው ፡ ምድር ፡ መረገጫ
አለም ፡ ዙፋንህ ፡ ነው ፡ ያንተ ፡ መቀመጫ
ሰማይም ፡ ያንተ ፡ ነው ፡ ምድርም ፡ ያንተ ፡ ነው ፡ ሁሉ ፡ ግዛትህ ፡ ነው
እግዚአብሔር ፡ አለ ፡ በማደሪያው
እግዚአብሔር ፡ አለ ፡ በዙፋኑ (፪x)

አዝ፦ እፁብ ፡ ነህ ፡ አንተ ፡ አንተ ፡ አትለወጥም
ግሩም ፡ ነህ ፡ አንተ ፡ ስራህም ፡ አያልቅም (፪x)

እግዚአብሔር ፡ አለ ፡ በማደሪያው
እግዚአብሔር ፡ አለ ፡ በዙፋኑ (፪x)

ይሁን ፡ ይሁን ፡ ብለህ ፡ የፈጠርከው ፡ ሁሉ
ጻድቅነትህን ፡ ይመሰክራሉ
እግዚአብሔር ፡ አለ ፡ እወቁት ፡ ይላሉ ፡ አክብሩት ፡ ይላሉ

እግዚአብሔር ፡ አለ ፡ በማደሪያው
እግዚአብሔር ፡ አለ ፡ በዙፋኑ (፪x)

አዝ፦ እፁብ ፡ ነህ ፡ አንተ ፡ አንተ ፡ አትለወጥም
ግሩም ፡ ነህ ፡ አንተ ፡ ስራህም ፡ አያልቅም (፪x)

እግዚአብሔር ፡ አለ ፡ በማደሪያው
እግዚአብሔር ፡ አለ ፡ በዙፋኑ (፪x)

ከፍ ፡ ከፍ ፡ ያለውን ፡ በሃይሉ ፡ አዋርዶ
የሃያላንንም ፡ ቀስታቸውን ፡ ሰብሮ
በክብር ፡ ይኖራል ፡ ዘላለም ፡ ይገዛል ፡ ዙፋኑ ፡ ይጸናል

እግዚአብሔር ፡ አለ ፡ በማደሪያው
እግዚአብሔር ፡ አለ ፡ በዙፋኑ (፪x)

አዝ፦ እፁብ ፡ ነህ ፡ አንተ ፡ አንተ ፡ አትለወጥም
ግሩም ፡ ነህ ፡ አንተ ፡ ስራህም ፡ አያልቅም (፪x)
እግዚአብሔር ፡ አለ ፡ በማደሪያው
እግዚአብሔር ፡ አለ ፡ በዙፋኑ ፡ (፪x)

በዘላለም ፡ ፍቅሩ ፡ ቀድሞ ፡ ባቀደው
አለምን ፡ ሊያድናት ፡ ኢየሱስን ፡ ላከው
ሃሳቡ ፡ ጸንታለች ፡ ማዳኑን ፡ አይተናል
ከሀጥያት ፡ እስራት ፡ ከሞትም ፡ ድነናል

እግዚአብሔር ፡ አለ ፡ በማደሪያው
እግዚአብሔር ፡ አለ ፡ በዙፋኑ (፪x)

አዝ፦ እፁብ ፡ ነህ ፡ አንተ ፡ አንተ ፡ አትለወጥም
ግሩም ፡ ነህ ፡ አንተ ፡ ስራህም ፡ አያልቅም (፪x)

እግዚአብሔር ፡ አለ ፡ በማደሪያው
እግዚአብሔር ፡ አለ ፡ በዙፋኑ (፪x)

ዙሪያው ፡ ገደል ፡ ሆኖ ፡ ግራ ፡ ቢገባህም
ጨለማው ፡ አይሎ ፡ መውጫው ፡ ቢጠፋም
እግዚአብሔር ፡ አለ ፡ እሱ ፡ አይተውህም ፡ እሱ ፡ አይጥልህም

ዙሪያው ፡ ገደል ፡ ሆኖ ፡ ግራ ፡ ቢገባሽም
ጨለማ ፡ አይሎ ፡ መውጫ ፡ ቢጠፋሽም
እግዚአብሔር ፡ አለ ፡ እሱ ፡ አይተውሽም ፡ እሱ ፡ አይጥልሽም

እግዚአብሔር ፡ አለ ፡ በማደሪያው
እግዚአብሔር ፡ አለ ፡ በዙፋኑ (፪x)

አዝ፦ እፁብ ፡ ነህ ፡ አንተ ፡ አንተ ፡ አትለወጥም
ግሩም ፡ ነህ ፡ አንተ ፡ ስራህም ፡ አያልቅም (፪x)