From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
አመታት ፡ አመታት ፡ አንተን ፡ አይለውጡህም (፪x)
ዘመናት ፡ ዘመናት ፡ አንተን ፡ አይለውጡህም (፪x)
ጥንትም ፡ ያለህ ፡ ዛሬም ፡ ለዘላለም
አምረህ ፡ ደምቀህ ፡ አሸብርቀህ
በዙፋንህ ፡ ላይ ፡ ጌታ ፡ ትኖራለህ
አምረህ ፡ ደምቀህ ፡ አሸብርቀህ
የአብርሃም ፡ አምላክ ፡ ዛሬም ፡ አላረጀህ
አምረህ ፡ ደምቀህ ፡ አሸብርቀህ
የይስሃቅ ፡ አምላክ ፡ ዛሬም ፡ አላረጀህ
የያዕቆብ ፡ አምላክ ፡ ዛሬም ፡ አላረጀህ
ስንቶቹ ፡ ነገሥታቶች ፡ ሲያልፉ ፡ ሲሻሩ
የእኛ ፡ አምላክ ፡ ብቻውን ፡ አለ ፡ በክብሩ
የነገሥታቶች ፡ ንጉሥ ፡ የጌቶች ፡ ጌታ
አይደክመው ፡ አይታክተው ፡ ሁሉን ፡ ሊረታ
አመታት ፡ አመታት ፡ አንተን ፡ አይለውጡህም (፪x)
ዘመናት ፡ ዘመናት ፡ አንተን ፡ አይለውጡህም (፪x)
ጥንትም ፡ ያለህ ፡ ዛሬም ፡ ለዘላለም
አምረህ ፡ ደምቀህ ፡ አሸብርቀህ
በዙፋንህ ፡ ላይ ፡ ጌታ ፡ ትኖራለህ
አምረህ ፡ ደምቀህ ፡ አሸብርቀህ ፡
የአብርሃም ፡ አምላክ ፡ ዛሬም ፡ አላረጀህ
አምረህ ፡ ደምቀህ ፡ አሸብርቀህ
የይስሃቅ ፡ አምላክ ፡ ዛሬም ፡ አላረጀህ
የያዕቆብ ፡ አምላክ ፡ ዛሬም ፡ አላረጀህ
በእነ ፡ አብርሃም ፡ ዘመን ፡ የነበረው
ሕዝቡን ፡ በምድረ ፡ በዳ ፡ የሚመራው
የዳዊት ፡ የሙሴ ፡ አምላክ ፡ መች ፡ ደከመው
የቀን ፡ የወሩ ፡ ብዛት ፡ አልለወጠው
አመታት ፡ አመታት ፡ አንተን ፡ አይለውጡህም (፪x)
ዘመናት ፡ ዘመናት ፡ አንተን ፡ አይለውጡህም (፪x)
ጥንትም ፡ ያለህ ፡ ዛሬም ፡ ለዘላለም
አምረህ ፡ ደምቀህ ፡ አሸብርቀህ
በዙፋንህ ፡ ላይ ፡ ጌታ ፡ ትኖራለህ
አምረህ ፡ ደምቀህ ፡ አሸብርቀህ
የአብርሃም ፡ አምላክ ፡ ዛሬም ፡ አላረጀህ
አምረህ ፡ ደምቀህ ፡ አሸብርቀህ
የይስሃቅ ፡ አምላክ ፡ ዛሬም ፡ አላረጀህ
የያዕቆብ ፡ አምላክ ፡ ዛሬም ፡ አላረጀህ
በሐዋርያት ፡ ነብያት ፡ ድንቅ ፡ የሰራው
መስራት ፡ አያቅተውም ፡ ዛሬም ፡ ያው ፡ ነው
የአጋንንትን ፡ ምሽግ ፡ ያፈራርሳል
ከጥንቱ ፡ የበለጠ ፡ ዛሬም ፡ ይሰራል
አመታት ፡ አመታት ፡ አንተን ፡ አይለውጡህም (፪x)
ዘመናት ፡ ዘመናት ፡ አንተን ፡ አይለውጡህም (፪x)
ጥንትም ፡ ያለህ ፡ ዛሬም ፡ ለዘላለም
አምረህ ፡ ደምቀህ ፡ አሸብርቀህ
በዙፋንህ ፡ ላይ ፡ ጌታ ፡ ትኖራለህ (፬x)
የአብርሃም ፡ አምላክ ፡ ዛሬም ፡ አላረጀህ
የይስሃቅ ፡ አምላክ ፡ ዛሬም ፡ አላረጀህ
የያዕቆብ ፡ አምላክ ፡ ዛሬም ፡ አላረጀህ
የያዕቆብ ፡ አምላክ ፡ ዛሬም ፡ አላረጀህ
|