የሮጡለትን ፡ ያዩታል (Yerotuleten Yayutal) - ሀና ፡ ተክሌ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ሀና ፡ ተክሌ
(Hana Tekle)

Hana Tekle 2.jpg


(2)

የዘለዓለም ፡ ፈጣሪ
(Yezelalem Fetari)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፭ (2013)
ቁጥር (Track):

(3)

ርዝመት (Len.): 5:26
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የሀና ፡ ተክሌ ፡ አልበሞች
(Albums by Hana Tekle)

ከአንተ ፡ በፊት ፡ የቆሰሉ ፡ ብዙ ፡ አሉ ፡ ለወንጌሉ
እንደ ፡ እኔና ፡ እንደ ፡ አንተ ፡ በነጻነት ፡ ዘመን ፡ ያልተፈጠሩ
ከአንቺ ፡ በፊት ፡ የተሰዉ ፡ ብዙ ፡ አሉ ፡ ለወንጌሉ
እንደ ፡ እኔና ፡ እንደ ፡ አንቺ ፡ በነጻነት ፡ ዘመን ፡ ያልተፈጠሩ

ከእኛ ፡ በፊት ፡ ብዙ ፡ አሉ ፡ የተሰዉ ፡ ለወንጌሉ
እንደ ፡ እኛ ፡ በነጻነት ፡ ዘመን ፡ ያልተፈጠሩ
ሳይሉ ፡ እጅ ፡ እግሬን ፡ ጨርቄን ፡ ማቄን ፡ በጽድቅ ፡ የኖሩ
በጌታ ፡ የተጉ ፡ ለጌታ ፡ የኖሩ ፡ በሰው ፡ የተጠሉ

አቤት ፡ የሮጡለትን ፡ ያዩታል ፡ ከወደላይ
የክብሩ ፡ ጌታ ፡ ሲያከብራቸው ፡ በሠማይ
አቤት ፡ ያዩታል ፡ ጌታን ፡ ፊት ፡ ለፊት
ሳያዩት ፡ ያመኑትን ፡ የናፈቁትን
በነፍሳቸው ፡ የጨከኑት ፡ በሥጋቸው ፡ ያከበሩት
አይገኝም ፡ አክሊላቸው ፡ በሠማይ ፡ ነው ፡ ክፍያቸው
አቤት ፡ የሮጡለትን ፡ ያዩታል ፡ ከወደላይ

ሆነው ፡ የባርነት ፡ ባሪያ ፡ ወጥተው ፡ ከሰውነት ፡ ተራ
የእኔ ፡ የሚሉት ፡ የሌላቸው ፡ ልሩጥ ፡ ለእኔም ፡ ማያቃቸው
ለወንጌል ፡ የቆሙ ፡ ለወንጌል ፡ የቀኑ
ገንዘብ ፡ የማይደፍራቸው ፡ ሰልፍ ፡ ብርታታቸው

አቤት ፡ የሮጡለትን ፡ ያዩታል ፡ ከወደላይ
የክብሩ ፡ ጌታ ፡ ሲያከብራቸው ፡ በሠማይ
አቤት ፡ ያዩታል ፡ ጌታን ፡ ፊት ፡ ለፊት
ሳያዩት ፡ ያመኑትን ፡ የናፈቁት
በነፍሳቸው ፡ የጨከኑት ፡ በሥጋቸው ፡ ያከበሩት
አይገኝም ፡ አክሊላቸው ፡ በሠማይ ፡ ነው ፡ ክፍያቸው
አቤት ፡ ያዩታል ፡ ጌታን ፡ ፊት ፡ ለፊት

ማነው ፡ ታዲያ ፡ የዘመኔ ፡ አርበኛ
ለጌታ ፡ ነገር ፡ ያልተኛ
ብድራቱን ፡ እዚህ ፡ ያልተቀበለ
እውነት ፡ ለወንጌል ፡ የጨከነ
በነጻነት ፡ ዘመን ፡ ራሱን ፡ የሰዋ
ለጥቅም ፡ ያልኖረ ፡ በእምነቱ ፡ የጸና

ማነው ፡ የዘመኔ ፡ ወንጌል ፡ ነጋሪ
በተግባር ፡ የታየ ፡ የጽድቅ ፡ ተባባሪ
ያልሆነ ፡ በፍፁም ፡ የነጻነት ፡ ባሪያ
ከቶ ፡ ያልተገኘ ፡ እዚህ ፡ ሲሉት ፡ እዚያ
ማነው ፡ የአቋም ፡ ሰው ፡ ዘመን ፡ ተሻጋሪ
ሰልፍ ፡ እየበረታ ፡ ወንጌሉን ፡ ዘማሪ

ማነው ፡ የዘመኔ ፡ ባለ ፡ አክሊል ፡ ተረኛ
ለራሱ ፡ ያልኖረ ፡ ከሥጋው ፡ ጠበኛ
ሞትን ፡ ጥቅሜ ፡ ብሎ ፡ በነፍሱ ፡ የጨከነ
ግራ ፡ ቀኝ ፡ ያላየ ፡ ለቃሉ ፡ የታመነ
ማነው ፡ የዘመኔ ፡ አርበኛ ፡ ማነው

አቤት ፡ የሮጡለትም ፡ ያዩታል ፡ ከወደላይ
የክብሩ ፡ ጌታ ፡ ሲያከብራቸው ፡ በሠማይ