ያለ ፡ ምክንያት (Yale Mekniyat) - ሀና ፡ ተክሌ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ሀና ፡ ተክሌ
(Hana Tekle)

Hana Tekle 2.jpg


(2)

የዘለዓለም ፡ ፈጣሪ
(Yezelalem Fetari)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፭ (2013)
ቁጥር (Track):

(10)

ርዝመት (Len.): 5:17
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የሀና ፡ ተክሌ ፡ አልበሞች
(Albums by Hana Tekle)

ስፈራ ፡ ስቸር ፡ ማልተነፍሰው ፡ ሚስጥሬ ፡ በዝቷል
እኔ ፡ ባልናገር ፡ የልብ ፡ ወዳጄ ፡ የውስጤን ፡ ያውቃል
እርሱ ፡ እንደሚያውቀኝ ፡ ሰው ፡ አያውቀኝም ፡ እንጂ
መቆም ፡ አልችልም ፡ እንኳን ፡ በንጉሥ ፡ በራሴም ፡ ደጅ

የምህረት ፡ ዓይኑ ፡ ዛሬም ፡ ያየኛል
አልሰለቸኝም ፡ ይፈልገኛል (፪x)

ፈላጊዬ ፡ መሃሪዬ ፡ ኢየሱስ ፡ ወዳጄ
አይዞሽ ፡ የሚለኝ ፡ እኔን ፡ ሚያበረታኝ
ነው ፡ የልብ ፡ ወዳጄ ፡ ነው ፡ ኢየሱስ
ኢየሱስ ፡ ኢየሱስ

እንዳትወደኝ ፡ በመልካምነቴ
ይህ ፡ አይደለም ፡ ማንነቴ
እንዳትጠላኝ ፡ ደግሞ ፡ በጥፋቴ
ፍቅር ፡ ነህ ፡ አያስችልህም ፡ አባቴ

ያለ ፡ ምክንያት ፡ ወደህ ፡ በምክንያት ፡ አትጠላም
ለምህረትህ ፡ ስፍር ፡ መለኪያ ፡ የለውም
የአንተ ፡ ፍቅር ፡ መነሺያው ፡ ከራስህ
የመውደድ ፡ ልብ ፡ የማያልቅብህ (፪x)
የእኔ ፡ ጌታ

ከወዳጅ ፡ ከፍቶ ፡ ልጅህ ፡ ድርሻዬን ፡ ብሎ ፡ እርም ፡ እንዳላለ
አልመች ፡ ቢለው ፡ የሸፈተበት ፡ አባቴን ፡ አለ
አባትነቱን ፡ የበደል ፡ ብዛት ፡ መች ፡ ይሽረዋል
ሁልን ፡ እረስቶ ፡ ደግሞ ፡ እንደገና ፡ ልጄ ፡ ይለዋል

በምህረት ፡ ዓይኑ ፡ ዛሬም ፡ ያየኛል
አልሰለቸኝም ፡ ይፈልገኛል
የምህረት ፡ ዓይኑ ፡ ዛሬም ፡ ያየኛል
አልሰለቸኝም ፡ ይፈልገኛል

ፈላጊዬ ፡ መሃሪዬ ፡ ኢየሱስ ፡ ወዳጄ
አይዞሽ ፡ የሚለኝ ፡ እኔን ፡ ሚያበረታኝ
ነው ፡ የልብ ፡ ወአጄ ፡ ነው ፡ ኢየሱስ
ኢየሱስ ፡ ኢየሱስ