Hana Tekle/Habte Semay/Yetadelen

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ

በአንተ ፡ የተጠራ ፡ ወገን ፡ በአንተ ፡ የተወደደ
ከጥፋት ፡ ባህር ፡ ንዳድ ፡ በስምህ ፡ የተጋረደ

ክብሩ ፡ ኢየሱስ ፡ የሆንክለት
መጠሪያ ፡ የዘውድ ፡ ስሙ
በኪዳንህ ፡ የሚራመድ
በደምህ ፡ የገባ ፡ ከደሙ
በክብርህ ፡ እሳት ፡ የሚነድ
በህልውናህ ፡ ዓለም
በእረፍት ፡ ጠል ፡ የረሰረሰ
ከህዝብህ ፡ በቀር ፡ የለም
የለም ፡ ከእኛ ፡ በቀር ፡ የለም
የለም ፡ ከህዝብህ ፡ በቀር ፡ የለም

የታደልን ፡ ህዝብ ፡ በአንተ ፡ ታየን
ተመረጥን ፡ ተወደድን
መስዋዕት ፡ በሆንክ ፡ በተነሳህ
ከሞት…..ከሞት ፡ አመለጥን

ክብራችን ፡ ነህ ፡ ሞገሳችን
ብንዘምርልህ ፡ ብንዘምርህ ፡ የማይደክመን
ለሰማዩም ፡ ለምድሩም ፡ መጠጊያ
የታመንብህ ፡ ጽኑ ፡ መጠለያ
ክብራችን ፡ ነህ ፡ ሞገሳችን
ብንዘምርልህ ፡ ብንተርክህ ፡ የማይደክመን
ለሰማዩም ፡ ለምድሩም ፡ መጠጊያ
የታመንብህ ፡ ጽኑ ፡ መጠለያ

እናመልክሃለን (x5)

በማይጠፋ ፡ ሕይወት ፡ በማይሞት
ገርስሰህ ፡ የዘላለምን ፡ ሞት
በብርሃንህ ፡ ብርሃን ፡ አሳየኸን
አንተው ፡ ባለህበት ፡ አሰፈርከን

ምን ፡ እንላለን? የሱስ ፡ ምን ፡ አለን?

ክበር ክበር ክበር (x3)

ክበር ፡ እንላለን
ንገስ ፡ ንገስ ፡ ንገስ
ንገስ ፡ እንላለን

ተሞኝተን ፡ አይደለም ፡ ምናመልክህ
ኢየሱስ ፡ ኢየሱስ ፡ የምንልህ
በደንብ ፡ ገብቶናል ፡ አንድ ፡ ፍቅርህ
ልንርቅ ፡ እኛ ፡ አንችልም ፡ ከእቅፍህ
ተሞኝቼ ፡ አይደለም ፡ የማመልክህ
ኢየሱስ ፡ ኢየሱስ ፡ ሁሌ ፡ ምልህ
ኧረ ፡ እኔስ ፡ ገብቶኛል ፡ አንድ ፡ ፍቅርህ
ልርቅ ፡ እኔ ፡ አልችልም ፡ ከእቅፍህ

ምን ፡ አለን ፡ ከአንተ ፡ ውጪ
እኛ ፡ ምን ፡ አለን ፡ ከአንተ ፡ ውጪ

ምንጠራው ፡ አንተን ፡ ነው ፡ ምንጠራው
ምናሳየው ፡ አንተን ፡ ነው ፡ ምናሳየው (x2)