በሩን ፡ ክፈቱ (Berun Kefetu) - ሀና ፡ ተክሌ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ሀና ፡ ተክሌ
(Hana Tekle)

Hana Tekle 3.jpg


(3)

ሀብተ ፡ ሰማይ
(Habte Semay)

ቁጥር (Track):

(1)


ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የሀና ፡ ተክሌ ፡ አልበሞች
(Albums by Hana Tekle)

ከሥም ፡ ሁሉ ፡ በላይ ፡ ኃያል ፡ ሥም ፡ አለው
በዚህ ፡ ሥም ፡ አምነን ፡ ድነናል ፡ ይኸው
ምስክሮቹ ፡ ነን ፡ ሕይወት ፡ ደርሶናል
ሰማይ ፡ ሲጎበኘን ፡ ለዓለም ፡ በርተናል

ተጠቅልለናል ፡ በክርስቶስ ፡ በኃያሉ ፡ ሥም
ከነበርንበት ፡ ዓለም ፡ የለንም
የሚበልጥ ፡ አይተን ፡ የሚደንቅ ፡ ክብር
ሰውን ፡ ኑ ፡ እንላለን ፡ አልፈን ፡ ከምድር

አምላክ ፡ ሥጋ ፡ ሆነ ፡ ለእኛ ፡ ማለደ
ከአብ ፡ አስታረቀን ፡ ስርየት ፡ ወረደ
ሕያው ፡ ልጆቹ ፡ ነን ፡ ዳግም ፡ ወልዶናል
ዘላለም ፡ ሲያገኘን ፡ ከሞት ፡ ጠፍተናል

ተጠቅልለናል ፡ በክርስቶስ ፡ በኃያሉ ፡ ሥም
ከነበርንበት ፡ ዓለም ፡ የለንም
የሚበልጥ ፡ አይተን ፡ የሚደንቅ ፡ ክብር
ሰውን ፡ ኑ ፡ እንላለን ፡ አልፈን ፡ ከምድር

እናንት ፡ መኳንንቶች ፡ በሩን ፡ ክፈቱ
የክብር ፡ ንጉሥ ፡ ይግባ ፡ በሩን ፡ ክፈቱ
ይሄ ፡ ንጉሥ ፡ ማነው ፡ እርሱ ፡ እግዚአብሔር ፡ ነው
የክብር ፡ ሁሉ ፡ ጌታ ፡ እርሱ ፡ እግዚአብሔር ፡ ነው

እርሱ ፡ እግዚአብሔር ፡ ነው (፪x)
እርሱ ፡ እግዚአብሔር

የክብር ፡ ሁሉ ፡ ጌታ ፡ የክብር ፡ ሁሉ ፡ ገዢ
እግዚአብሔር ፡ ነው ፡ ብርቱና ፡ ኃያል (፪x)
የሰማይ ፡ የምድሩ ፡ የልዑላን ፡ ጌታ
እግዚአብሔር ፡ ነው ፡ ብርቱና ፡ ኃያል (፪x)

ሆሆ ፡ ኃያሉ ፡ እግዚአብሔር
እርሱ ፡ እኛን ፡ ጎበኘ
እንድንዘምርለት ፡ ዙሪያው ፡ ሰበሰበን

ሆሆ ፡ እግዚአብሔር ፡ ረዳን
እግዚአብሔር ፡ አሰበን
በየደረስንበት ፡ ኃያል ፡ መዝሙር ፡ ሆነን

ምሥጋና ፡ የተገባው ፡ እርሱ ፡ ነው
ውዳሴ ፡ የተገባው ፡ እርሱ ፡ ነው
ለእኛ ፡ ታየን ፡ መድኃኔዓለም
እንደርሱ ፡ የለም ፡ ዘላለም
ለእኛ ፡ ተገለጠ ፡ መድኃኔዓለም
እንደርሱ ፡ የለም ፡ ዘላለም

ዝማሬ ፡ የተገባው ፡ እርሱ ፡ ነው
ስግደትም ፡ የተገባው ፡ እርሱ ፡ ነው
ለእኛ ፡ ታየን ፡ መድኃኔዓለም
እንደርሱ ፡ የለም ፡ ዘላለም
ለእኛ ፡ ተገለጠ ፡ መድኃኒዓለም
እንደሱ ፡ የለም ፡ ዘላለም