ምህረትን ፡ ትወዳለህ (Mehereten Tewedaleh) - ኃይለኢየሱስ ፡ ታደሰ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ኃይለኢየሱስ ፡ ታደሰ
(Haileyesuse Taddesse)

Haileyesuse Taddesse 1.jpg


(1)

አየሁ
(Ayehu)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፮ (2013)
ቁጥር (Track):

(9)


ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የኃይለኢየሱስ ፡ ታደሰ ፡ አልበሞች
(Albums by Haileyesuse Taddesse)

በመንገድህ ፡ አግኘኝ ፡ ጌታ ፡ እንደ ፡ ሀሳብህ
ለትጐበኘኝ ፡ ስትመጣ ፡ እንዳልጠፋ ፡ ከፊትህ
ፀጋህን ፡ አብዛልኝ ፡ ኢየሱስ ፡ በሕይወቴ
መንፈስህ ፡ ያግዘኝ ፡ ይጽና ፡ መሰረቴ (፪x)

አዝ፦ ምህረትን ፡ ትወዳለህና
ብርታትን ፡ ትሰጣለህና
እኔም ፡ ልታሰብ ፡ ጌታ
ኃይል ፡ ይብዛልኝ ፡ ልበርታ
ኑሮዬ ፡ አንተን ፡ ይምሰልህ
ከፍ ፡ ያድርግህ ፡ ያክብርህ ፡ አሜን

ስለ ፡ እኔ ፡ ነፍስህን ፡ ልትሰጥ ፡ አልሰሰትክምና
እዳዬን ፡ ሁሉ ፡ ልትከፍል ፡ ተችሎሀልና
እኔም ፡ ለመውደድህ ፡ ልሁን ፡ እንደልብህ
አንተን ፡ መፍራት ፡ ሙላኝ ፡ ዝቅ ፡ ልበልልህ (፪x)

አዝ፦ ምህረትን ፡ ትወዳለህና
ብርታትን ፡ ትሰጣለህና
እኔም ፡ ልታሰብ ፡ ጌታ
ኃይል ፡ ይብዛልኝ ፡ ልበርታ
ኑሮዬ ፡ አንተን ፡ ይምሰልህ
ከፍ ፡ ያድርግህ ፡ ያክብርህ ፡ አሜን

በመቅደስህ ፡ ቀድሰኝ ፡ በእሣትህ ፡ አንጥረኝ
የማትወደው ፡ ከእኔ ፡ ይቆረጥ ፡ እንዳሻህ ፡ አበጃጀኝ
ለእኔም ፡ የሻለኛል ፡ በእጅህ ፡ መቀረፁ
ኋላ ፡ ሞልቶ ፡ ይፈሣል ፡ ከአንተ ፡ በረከቱ (፪x)

አዝ፦ ምህረትን ፡ ትወዳለህና
ብርታትን ፡ ትሰጣለህና
እኔም ፡ ልታሰብ ፡ ጌታ
ኃይል ፡ ይብዛልኝ ፡ ልበርታ
ኑሮዬ ፡ አንተን ፡ ይምሰልህ
ከፍ ፡ ያድርግህ ፡ ያክብርህ ፡ አሜን

ድንጋዩ ፡ ልብ ፡ ከእኔ ፡ ይውጣ ፡ ስጋ ፡ ይሁንልኝ
የቀናውን ፡ መንፈስህን ፡ በውስጤ ፡ አድስልኝ
ክርስቲያን ፡ ከተባልኩ ፡ በአንተ ፡ ከተጠራሁ
እንደ ፡ ሀሳብህ ፡ ኖሬ ፡ ማለፍን ፡ እሻለሁ (፪x)

አዝ፦ ምህረትን ፡ ትወዳለህና
ብርታትን ፡ ትሰጣለህና
እኔም ፡ ልታሰብ ፡ ጌታ
ኃይል ፡ ይብዛልኝ ፡ ልበርታ
ኑሮዬ ፡ አንተን ፡ ይምሰልህ
ከፍ ፡ ያድርግህ ፡ ያክብርህ ፡ አሜን (፪x)