አመልካለሁ (Amelkalehu) - ኃይለኢየሱስ ፡ ታደሰ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ኃይለኢየሱስ ፡ ታደሰ
(Haileyesuse Taddesse)

Haileyesuse Taddesse 1.jpg


(1)

አየሁ
(Ayehu)

ዓ.ም. (Year): ፳፻፮ (2013)
ቁጥር (Track):

(8)


ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የኃይለኢየሱስ ፡ ታደሰ ፡ አልበሞች
(Albums by Haileyesuse Taddesse)

 
አዝ፦ አንተን ፡ ታምኜ ፡ ኽረ ፡ ምን ፡ ሆኜ
አንተን ፡ ታምኜ ፡ ጌታዬ ፡ ኧረ ፡ ምን ፡ ሆኜ
አንተን ፡ ታምኜ ፡ ኧረ ፡ ምን ፡ ሆኜ
አንተን ፡ ጠበኩኝ ፡ መቼ ፡ አፈርኩኝ
አንተን ፡ ጠበኩኝ ፡ አባቴ ፡ መቼ ፡ አፈርኩኝ
አንተን ፡ ጠበኩኝ ፡ መቼ ፡ አፈርኩኝ

ተማመንኩብህ ፡ በአንተ ፡ አባቴ
ከጐኔ ፡ ሆነህ ፡ ሥትሞላው ፡ ቤቴን
ምንስ ፡ አገኘኝ ፡ አንተን ፡ ታምኜ
ኽረ ፡ ምን ፡ ልሆን ፡ አለህ ፡ አዳኜ
አለህ ፡ አዳኜ (፬x)

የረዳኝን ፡ ያገዘኝን ፡ እግዚአብሔርን ፡ አመልካለሁ (፪x)
የረዳኝ ፡ አቅም ፡ የሆነከኝ ፡ እግዚአብሔርን ፡ አመልካለሁ (፪x)

ስንቴ ፡ ረዳኽኝ ፡ ስንቴ ፡ አገዝከኝ
ከጐኔ ፡ ሆነህ ፡ እያበረታኽኝ
ባለቀ ፡ ነገር ፡ ጣልቃ ፡ እየገባህ
እዚህ ፡ አደረስከኝ ፡ እጆቼን ፡ ይዘህ
እጆቼን ፡ ይዘህ (፬x)

አዝ፦ አንተን ፡ ታምኜ ፡ ኽረ ፡ ምን ፡ ሆኜ
አንተን ፡ ታምኜ ፡ ጌታዬ ፡ ኧረ ፡ ምን ፡ ሆኜ
አንተን ፡ ታምኜ ፡ ኧረ ፡ ምን ፡ ሆኜ
አንተን ፡ ጠበኩኝ ፡ መቼ ፡ አፈርኩኝ
አንተን ፡ ጠበኩኝ ፡ አባቴ ፡ መቼ ፡ አፈርኩኝ
አንተን ፡ ጠበኩኝ ፡ መቼ ፡ አፈርኩኝ

ስንቴ ፡ ረዳኽኝ ፡ ስንቴ ፡ አገዝከኝ
ከጐኔ ፡ ሆነህ ፡ እያበረታኽኝ
ባለቀ ፡ ነገር ፡ ጣልቃ ፡ እየገባህ
እዚህ ፡ አደረስከኝ ፡ እጆቼን ፡ ይዘህ
እጆቼን ፡ ይዘህ (፬x)

የረዳኝን ፡ ያገዘኝን ፡ እግዚአብሔርን ፡ አመልካለሁ (፪x)
የረዳኝ ፡ አቅም ፡ የሆነከኝ ፡ እግዚአብሔርን ፡ አመልካለሁ (፪x)
ነገሮች ፡ ባይቀየሩም ፡ አመልካለሁ
ቢጐድልም ፡ ቢሞላም ፡ አመልካለሁ
እርሱን ፡ ታምኛለሁ ፡ አመልካለሁ
በፍፁም ፡ አልሰጋም ፡ አመልካለሁ
ነገሮች ፡ ባይቀየሩም ፡ አመልካለሁ
ያስብኩት ፡ ባይሞላም ፡ አመልካለሁ
ጌታን ፡ ታምኛለሁ ፡ አመልካለሁ
በጭራሽ ፡ አልሰጋም ፡ አመልካለሁ
ነገሮች ፡ ባይቀየሩም ፡ አመልካለሁ
ቢጐድልም ፡ ቢሞላም ፡ አመልካለሁ
እርሱን ፡ ታምኛለሁ ፡ አመልካለሁ
በፍፁም ፡ አልሰጋም ፡ አመልካለሁ
አመልካለሁ (፰x)