በአማልክቶች ፡ በካከል (Beamalektoch Mekakel) - ግሩም ፡ ታደሰ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ግሩም ፡ ታደሰ
(Girum Tadesse)

Girum Tadesse 3.jpg


(3)

ከልቤ ፡ የፈለቀ
(Kelebie Yefeleqe)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፫ (2011)
ቁጥር (Track):

፲ ፩ (11)


ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የግሩም ፡ ታደሰ ፡ አልበሞች
(Albums by Girum Tadesse)

 
ብዙዎች ፡ ተነሱ ፡ ሃያላን ፡ የተባሉ
በጦር ፡ በሰልፍ ፡ ብዛት ፡ ስማቸውን ፡ ያስጠሩ
አልኖሩም ፡ አለፉ ፡ ሞት ፡ አሸነፋቸው
ሃያል ፡ አንተ ፡ ብቻ ፡ እያሸነፍካቸው

አዝ፦ በአምልክቶች ፡ መካከል ፡ እንደአንተ ፡ የለም
ንጉሥ ፡ ሆይ ፡ ንገሥ ፡ ዘለዓለም (፪x)
በአምልክቶች ፡ መካከል ፡ እንደአንተ ፡ የለም
ጌታ ፡ ሆይ ፡ ክበር ፡ ዘለዓለም (፪x)

ታቦቱንም ፡ ወሰዱና ፡ አቋቆሙት ፡ ከዳጐን ፡ ጋር
መቼ ፡ ችሎት ፡ ፊቱ ፡ ቆመ
ያማረው ፡ ዳጐን ፡ ተሰባበረ (፪x)

አዝ፦ በአምልክቶች ፡ መካከል ፡ እንደአንተ ፡ የለም
ንጉሥ ፡ ሆይ ፡ ንገሥ ፡ ዘለዓለም (፪x)
በአምልክቶች ፡ መካከል ፡ እንደአንተ ፡ የለም
ጌታ ፡ ሆይ ፡ ክበር ፡ ዘለዓለም (፪x)

ይህ ፡ ታላቅ ፡ አምላክ ፡ ይዤ
ለማይሰማ ፡ አምላክ ፡ አልሰግድም
በእቶኑ ፡ እሳት ፡ ብጣል ፡ እንኳን
ስለሚወደኝ ፡ ይደርስልኛል
ስለሚወደኝ ፡ ፈጥኖ ፡ ይመጣል

አዝ፦ በአምልክቶች ፡ መካከል ፡ እንደአንተ ፡ የለም
ንጉሥ ፡ ሆይ ፡ ንገሥ ፡ ዘለዓለም (፪x)
በአምልክቶች ፡ መካከል ፡ እንደአንተ ፡ የለም
ጌታ ፡ ሆይ ፡ ክበር ፡ ዘለዓለም (፪x)

ከባዖል ፡ ነቢያት ፡ ጋራ ፡ ሲወዳደር ፡ ተዐምር ፡ ሰራ
ሰምቶ ፡ በእሳት ፡ መለሰ
ከእነሱ ፡ አምላክ ፡ የእኔ ፡ በለጠ
ከእነሱ ፡ አምላክ ፡ ኢየሱስ ፡ በለጠ

አዝ፦ በአምልክቶች ፡ መካከል ፡ እንደአንተ ፡ የለም
ንጉሥ ፡ ሆይ ፡ ንገሥ ፡ ዘለዓለም (፪x)
በአምልክቶች ፡ መካከል ፡ እንደአንተ ፡ የለም
ጌታ ፡ ሆይ ፡ ክበር ፡ ዘለዓለም (፪x)

ብዙዎች ፡ ተነሱ ፡ ሃያላን ፡ የተባሉ
በጦር ፡ በሰልፍ ፡ ብዛት ፡ ስማቸውን ፡ ያስጠሩ
አልኖሩም ፡ አለፉ ፡ ሞት ፡ አሸነፋቸው
ሃያል ፡ አንተ ፡ ብቻ ፡ እያሸነፍካቸው