በግ ፡ የሆነከው (Beg Yehonkew) - ጌታያውቃል ፡ እና ፡ ብሩክታዊት

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ጌታያውቃል ፡ እና ፡ ብሩክታዊት
(Getayawkal & Birucktawit)

Getayawkal and Birucktawit 2006.jpeg

፳ ፻ ፮
(2006)

የ፲፩ኛው ፡ ሰዓት ፡ የጸሎት ፡ ጥሪ
(Ye11gnaw Seat Yetselot Teri)

ዓ.ም. (Year): ፲ ፱ ፻ ፺ ፰ (2006)
ቁጥር (Track):

(4)


ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የጌታያውቃል ፡ እና ፡ ብሩክታዊት ፡ አልበሞች
(Albums by Getayawkal & Birucktawit)

 
"በነገር ፡ ሁሉ ፡ በጸሎትና ፡ በምልጃ ፡ ከምሥጋና ፡ ጋር
በእግዚአብሔር ፡ ዘንድ ፡ ልመናችሁን ፡ አስታውቁ ፡ እንጂ
በአንዳች ፡ አትጨነቁ"

ስለ ፡ እራሴ ፡ ስለ ፡ ግሌ
ስለ ፡ ቤቴ ፡ ስለ ፡ አገሬ
ስለ ፡ ኑሮ ፡ ስለ ፡ ሕይወት
ስለ ፡ ያዝኩት ፡ አገልግሎት
የማዋይህ ፡ አለኝና ፡ ልምበርከክ ፡ ፊትህ ፡ እንደገና
የማዋይህ ፡ አለኝና ፡ ልምበርከክ ፡ ፊትህ ፡ እንደገና (፪x)

የእግዚአብሔር ፡ በግ ፡ የሆንከው
ልቤን ፡ በፍቅርህ ፡ ያደስከው
ጓዴ/ጌታ ፡ ኢየሱስ ፡ እስቲ ፡ ና
የማዋይህ ፡ አለኝና (፪x)

"ያዕቆብ ፡ ግን ፡ ለብቻው ፡ ቀረ
አንድ ፡ ሰው ፡ እስኪነጋ ፡ ድረስ ፡ ይታገለው ፡ ነበር
እንዳላሸነፈውም ፡ ባየ ፡ ጊዜ ፡ የጭኑን ፡ ሽሉዳ??? ፡ ነካው
ያዕቆብም ፡ የጭኑን ፡ ??? ፡ ሲታገለው ፡ ደነዘዘ
እንዲህም ፡ አለው ፡ 'ሊነጋ ፡ አቅላልቷልና ፡ ልቀቀኝ'
እርሱም ፡ 'ካልባረከኝ ፡ አለቅህም' ፡ አለው
እንዲህም ፡ አለው ፡ 'ስምህ ፡ ማነው?'
እርሱም ፡ 'ያዕቆብ ፡ ነኝ ፡ አለው'
'ከእንግዲህ ፡ ወዲህ ፡ ስምህ ፡ እስራኤል
ይባላል ፡ እንጂ ፡ ያዕቆብ ፡ አይባልም'
በዚያም ፡ ስፍራ ፡ ባረከው።"

በረከትህን ፡ ልጥራ ፡ በእኔ ፡ ላይ ፡ በዚህ ፡ ማለዳ
በረከትህን ፡ ልጥራ ፡ በቤቴ ፡ ላይ ፡ በዚህ ፡ ማለዳ
በረከትህን ፡ ልጥራ ፡ በአገሬ ፡ ላይ ፡ በዚህ ፡ ማለዳ
በረከትህን ፡ ልጥራ ፡ ቤተሰቤን ፡ ላይ ፡ በዚህ ፡ ማለዳ
በረከትህን ፡ ልጥራ ፡ ስራዬ ፡ ላይ ፡ በዚህ ፡ ማለዳ
በረከትህን ፡ ልጥራ ፡ ትምህርቴ ፡ ላይ ፡ በዚህ ፡ ማለዳ
በረከትህን ፡ ልጥራ ፡ ትዳሬ ፡ ላይ ፡ በዚህ ፡ ማለዳ
በረከትህን ፡ ልጥራ ፡ በእኔነቴ ፡ በዚህ ፡ ማለዳ

ካልባረከኝ ፡ አለቅህም (፬x)
ካልዳሰስከኝ ፡ አለቅህም (፪x)
ካልፈወስከኝ ፡ አለቅህም (፪x)
ካለወጥከኝ ፡ አለቅህም (፪x)
ካላደስከኝ ፡ አለቅህም (፪x)
ካልባረከኝ ፡ አለቅህም (፪x)