ምሥጋና (Mesgana) - ጌታያውቃል ፡ ግርማይ ፡ እና ፡ ብሩክታዊት ፡ አሰፋ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ጌታያውቃል ፡ ግርማይ ፡ እና ፡ ብሩክታዊት ፡ አሰፋ
(Getayawkal and Birucktawit)

Getayawkal and Birucktawit 1.jpg


(1)

ምድር ፡ አለፈላት
(Meder Alefelat)

ዓ.ም. (Year): ፲ ፱ ፻ ፺ ፭ (2002)
ቁጥር (Track):

(5)

ርዝመት (Len.): 7:21
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የጌታያውቃል ፡ ግርማይ ፡ እና ፡ ብሩክታዊት ፡ አሰፋ ፡ አልበሞች
(Albums by Getayawkal and Birucktawit)

አዝ፦ በማለዳ ፡ ምሥጋናዬን ፡ አበዛለሁ
በቀትርም ሌላ ፡ ክብር ፡ እጨምራለሁ
ጊዜው ፡ መምሸቱ ፡ ውድቅት ፡ ሌሊቱ
አያግደኝም ፡ ከመቅረብ ፡ ፊቱ
ሥሙን ፡ ልባርከው ፡ ሁሌ ፡ ጠራዋለሁ
ክብር ፡ እያበዛሁ ፡ አስደስተዋለሁ
ሥሙን ፡ ልባርከው ፡ ሁሌ ፡ ጠራዋለሁ
ድምጼን ፡ እያሰማሁ ፡ አስደስተዋለሁ

አፌን ፡ በምሥጋና ፡ ሞልተኸዋልና
እግዚአብሔር ፡ እኔ ፡ ልባርክህ (፪x)
እናገር ፡ የምችለውን ፡ ይህን ፡ ነውና
እግዚአብሔር ፡ እኔ ፡ ልባርክህ (፪x)
ያዘነ ፡ በፊትህ ፡ አይገኝምና
እግዚአብሔር ፡ እኔ ፡ ልባርክህ (፪x)
በፊትህ ፡ ቃል ፡ ደስታ ፡ ይጠግባልና
እግዚአብሔር ፡ እኔ ፡ ልባርክህ (፪x)

አዝ፦ በማለዳ ፡ ምሥጋናዬን ፡ አበዛለሁ
በቀትርም ፡ ሌላ ፡ ክብር ፡ እጨምራለሁ
ጊዜው ፡ መምሸቱ ፡ ውድቅት ፡ ሌሊቱ
አያግደኝም ፡ ከመቅረብ ፡ ፊቱ
ሥሙን ፡ ልባርከው ፡ ሁሌ ፡ ጠራዋለሁ
ክብር ፡ እያበዛሁ ፡ አስደስተዋለሁ
ሥሙን ፡ ልባርከው ፡ ሁሌ ፡ ጠራዋለሁ
ድምጼን ፡ እያሰማሁ ፡ አስደስተዋለሁ

የጐበጠው ፡ ሁሉ ፡ ቀና ፡ ይላልና
እግዚአብሔር ፡ እኔ ፡ ልባርክህ (፪x)
ለሰው ፡ የማይቻል ፡ ይቻልሃልና
እግዚአብሔር ፡ እኔ ፡ ልባርክህ (፪x)
ለቃልህ ፡ የማይታዘዝ ፡ አንድም ፡ የለምና
እግዚአብሔር ፡ እኔ ፡ ልባርክህ (፪x)
ብቻህን ፡ ተዓምራት ፡ ታደርጋለህና
እግዚአብሔር ፡ እኔ ፡ ልባርክህ (፪x)

አዝ፦ በማለዳ ፡ ምሥጋናዬን ፡ አበዛለሁ
በቀትርም ፡ ሌላ ፡ ክብር ፡ እጨምራለሁ
ጊዜው ፡ መምሸቱ ፡ ውድቅት ፡ ሌሊቱ
አያግደኝም ፡ ከመቅረብ ፡ ፊቱ
ሥሙን ፡ ልባርከው ፡ ሁሌ ፡ ጠራዋለሁ
ክብር ፡ እያበዛሁ ፡ አስደስተዋለሁ
ሥሙን ፡ ልባርከው ፡ ሁሌ ፡ ጠራዋለሁ
ድምጼን ፡ እያሰማሁ ፡ አስደስተዋለሁ

ሕዝብህ ፡ ወደ ፡ እረፍት ፡ ይገባልና
እግዚአብሔር ፡ እኔ ፡ ልባርክህ (፪x)
እርዳታህም ፡ ከላይ ፡ ይመጣልና
እግዚአብሔር ፡ እኔ ፡ ልባርክህ (፪x)
በሰንበትም ፡ ችግር ፡ አይገኝምና
እግዚአብሔር ፡ እኔ ፡ ልባርክህ (፪x)
ሁሉ ፡ በሚያርፍበት ፡ ትሰራለህና
እግዚአብሔር ፡ እኔ ፡ ልባርክህ (፪x)

አዝ፦ በማለዳ ፡ ምሥጋናዬን ፡ አበዛለሁ
በቀጥትርም ፡ ሌላ ፡ ክብር ፡ እጨምራለሁ
ጊዜው ፡ መምሸቱ ፡ ውድቅት ፡ ሌሊቱ
አያግደኝም ፡ ከመቅረብ ፡ ፊቱ
ሥሙን ፡ ልባርከው ፡ ሁሌ ፡ ጠራዋለሁ
ክብር ፡ እያበዛሁ ፡ አስደስተዋለሁ
ሥሙን ፡ ልባርከው ፡ ሁሌ ፡ ጠራዋለሁ
ድምጼን ፡ እያሰማሁ ፡ አስደስተዋለሁ