አትገመትም (Ategemetem) - ጌታያውቃል ፡ ግርማይ ፡ እና ፡ ብሩክታዊት ፡ አሰፋ

From WikiMezmur: Mezmur Lyrics
Jump to: navigation, search
ጌታያውቃል ፡ ግርማይ ፡ እና ፡ ብሩክታዊት ፡ አሰፋ
(Getayawkal and Birucktawit)

Getayawkal and Birucktawit 1.jpg


(1)

ምድር ፡ አለፈላት
(Meder Alefelat)

ዓ.ም. (Year): ፲ ፱ ፻ ፺ ፭ (2002)
ቁጥር (Track):

(2)


ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የጌታያውቃል ፡ ግርማይ ፡ እና ፡ ብሩክታዊት ፡ አሰፋ ፡ አልበሞች
(Albums by Getayawkal and Birucktawit)

አዝ፦ አተገመትም ፡ በእኔ ፡ ቃላት ፡ ብዛት
አትወሰንም ፡ በአእምሮ ፡ ስፋት
አትገመትም ፡ በሺህ ፡ ቃላት ፡ ብዛት
አትወሰንም ፡ በጠቢባን ፡ ጥበብ
አንተ ፡ ከሁሉ ፡ በላይ ፡ ነህ ፤ በላይ ፡ ነህ (፪x)

የችግር ፡ ቋጠሮ ፡ ውስብስብ ፡ ሲልብኝ
መግቢያ ፡ መውጫ ፡ ጠፍቶህ ፡ ግራ ፡ ሲያጋባኝ
አንተ ፡ ከሁሉ ፡ በላይ ፡ ነህ
ደግሞ ፡ ሲፈታታ ፡ ችግር ፡ ሁሉ ፡ ሲተን
የትላንት ፡ ጨለማ ፡ እንደጉም ፡ ሲበተን
አንተ ፡ ከሁሉ ፡ በላይ ፡ ነህ

አዝ፦ አተገመትም ፡ በእኔ ፡ ቃላት ፡ ብዛት
አትወሰንም ፡ በአእምሮ ፡ ስፋት
አትገመትም ፡ በሺህ ፡ ቃላት ፡ ብዛት
አትወሰንም ፡ በጠቢባን ፡ ጥበብ
አንተ ፡ ከሁሉ ፡ በላይ ፡ ነህ ፤ በላይ ፡ ነህ (፪x)

አንተን ፡ እንዳላመልክ ፡ ከፍታው ፡ ዝቅታ
ከቶ ፡ አያግደኝም ፡ አይጠፋኝ ፡ ዕልልታ
አንተ ፡ ከሁሉ ፡ በላይ ፡ ነህ
ውስጤ ፡ ቅኔ ፡ ሞልቷል ፡ ከገጠመኝ ፡ በላይ
አምላኬ ፡ እግዚአብሔር ፡ ነህና ፡ ኤልሻዳይ
አንተ ፡ ከሁሉ ፡ በላይ ፡ ነህ

አዝ፦ አተገመትም ፡ በእኔ ፡ ቃላት ፡ ብዛት
አትወሰንም ፡ በአእምሮ ፡ ስፋት
አትገመትም ፡ በሺህ ፡ ቃላት ፡ ብዛት
አትወሰንም ፡ በጠቢባን ፡ ጥበብ
አንተ ፡ ከሁሉ ፡ በላይ ፡ ነህ ፤ በላይ ፡ ነህ (፪x)

ሁሉም ፡ ነገር ፡ ጠፍቶ ፡ በቤቴ ፡ የሚበላ
ያልጠበኩት ፡ ነገር ፡ ሲሆንብኝ ፡ ሌላ
አንተ ፡ ከሁሉ ፡ በላይ ፡ ነህ
ደግሞ ፡ በጐጆዬ ፡ በረከት ፡ ሲሞላ
ሁሉም ፡ ነገር ፡ ሞልቶ ፡ ሲተርፈኝ ፡ ለሌላ
አንተ ፡ ከሁሉ ፡ በላይ ፡ ነህ

አዝ፦ አተገመትም ፡ በእኔ ፡ ቃላት ፡ ብዛት
አትወሰንም ፡ በአእምሮ ፡ ስፋት
አትገመትም ፡ በሺህ ፡ ቃላት ፡ ብዛት
አትወሰንም ፡ በጠቢባን ፡ ጥበብ
አንተ ፡ ከሁሉ ፡ በላይ ፡ ነህ ፤ በላይ ፡ ነህ (፪x)

ሲሞላ ፡ ዘምሬ ፡ ሲጐድል ፡ ላላለቅስ
በምንም ፡ ሁኔታ ፡ አምልኮ ፡ አልቀንስም
አንተ ፡ ከሁሉም ፡ በላይ ፡ ነህ
እታመንሃለሁ ፡ በምሥጋና ፡ ሆኜ
ድል ፡ እንደምትሰጠኝ ፡ በስምህ ፡ አምኜ
አንተ ፡ ከሁሉም ፡ በላይ ፡ ነህ

አዝ፦ አተገመትም ፡ በእኔ ፡ ቃላት ፡ ብዛት
አትወሰንም ፡ በአእምሮ ፡ ስፋት
አትገመትም ፡ በሺህ ፡ ቃላት ፡ ብዛት
አትወሰንም ፡ በጠቢባን ፡ ጥበብ
አንተ ፡ ከሁሉ ፡ በላይ ፡ ነህ ፤ በላይ ፡ ነህ (፪x)