በምህረትህ ፡ ተከልዬ (Bemehereteh Tekeleyie) - ፌቨን ፡ ብርሃኑ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ፌቨን ፡ ብርሃኑ
(Feven Berhanu)

Feven Berhanu 1.jpg


(1)

በምህረትህ ፡ ተከልዬ
(Bemehereteh Tekeleyie)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፬ (2012)
ቁጥር (Track):

(1)

ርዝመት (Len.): 4:37
ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የፌቨን ፡ ብርሃኑ ፡ አልበሞች
(Albums by Feven Berhanu)

በምህረትህ ፡ ተከልዬ
አልፌአለው ፡ ሁሉን ፡ ችዬ
ስላለኸኝ ፡ ዋስትናዬ
ከቶ ፡ አልፈራም ፡ የነገዬን

በጨለመው(ባስጨናቂው) ፡ ሌሊት ፡ ያኔ ፡ አሳልፈኽ
ቀን ፡ ካወጣህልኝ ፡ እንባዬን ፡ አብሰኽ
ነገን ፡ እንዴት ፡ ልፍራ ፡ ልስጋ ፡ ለመኖሬ
አንተ ፡ እያለኸኝ ፡ የዘላለም ፡ ክብሬ

እንካ ፡ ምሥጋናዬን ፡ እንካ (፫x)
እንካ ፡ አምልኮዬን ፡ እንካ (፫x)
እንካ ፡ ሽብሸባዬን ፡ እንካ (፫x)
እንካ ፡ ዕልልታዬን ፡ እንካ (፫x)

ይገባሃልና ፡ ጌታ ፡ ይገባሃልና
ይገባሃልና ፡ ኢየሱስ ፡ ይገባሃልና

በምህረትህ ፡ ተከልዬ
አልፌአለው ፡ ሁሉን ፡ ችዬ
ስላለኸኝ ፡ ዋስትናዬ
ከቶ ፡ አልፈራም ፡ የነገዬን

ጠላት ፡ በዙሪያዬ ፡ ቢያገሳ ፡ እንዳንበሳ
ከለላዬን ፡ ሳይ ፡ ቢጮህ ፡ ቢያገሳ
የሰማዩ ፡ አባቴ ፡ እኔን ፡ ከልሎኛል
ክፉ ፡ አንዳያገኘኝ ፡ ቅጥር ፡ ቀጥሮልኛል

እንካ ፡ ምሥጋናዬን ፡ እንካ (፫x)
እንካ ፡ አምልኮዬን ፡ እንካ (፫x)
እንካ ፡ ሽብሸባዬን ፡ እንካ (፫x)
እንካ ፡ ዕልልታዬን ፡ እንካ (፫x)

ይገባሃልና ፡ ጌታ ፡ ይገባሃልና
ይገባሃልና ፡ ኢየሱስ ፡ ይገባሃልና

በምህረትህ ፡ ተከልዬ
አልፌአለው ፡ ሁሉን ፡ ችዬ
ስላለኸኝ ፡ ዋስትናዬ
ከቶ ፡ አልፈራም ፡ የነገዬን

ባሸናፊው ፡ ጌታ ፡ ሁሉን ፡ ነገር ፡ ጥዬ
በመንፈሱ ፡ ብርታት ፡ ቆምኩኝ ፡ ቀና ፡ ብዬ
በሃይሌ ፡ አይደለም ፡ ወይም ፡ በብርታቴ
ያቆመኝ ፡ ጌታ ፡ ነው ፡ የሆነኝ ፡ ጉልበቴ

እንካ ፡ ምሥጋናዬን ፡ እንካ (፫x)
እንካ ፡ አምልኮዬን ፡ እንካ (፫x)
እንካ ፡ ሽብሸባዬን ፡ እንካ (፫x)
እንካ ፡ ዕልልታዬን ፡ እንካ (፫x)

ይገባሃልና ፡ ጌታ ፡ ይገባሃልና
ይገባሃልና ፡ ኢየሱስ ፡ ይገባሃልና

በምህረትህ ፡ ተከልዬ
አልፌአለው ፡ ሁሉን ፡ ችዬ
ስላለኸኝ ፡ ዋስትናዬ
ከቶ ፡ አልፈራም ፡ የነገዬን