ፍቅሩ ፡ አያረጅም (Feqru Ayarejem) - ኢየሩሳሌም ፡ ነጊያ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ኢየሩሳሌም ፡ ነጊያ
(Eyerusalem Negiya)

Eyerusalem Negiya 2.jpg


(2)

ቀን ፡ ሳለ
(Qen Sale)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፬ (2012)
ቁጥር (Track):

(2)


ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የኢየሩሳሌም ፡ ነጊያ ፡ አልበሞች
(Albums by Eyerusalem Negiya)

እግዚአብሔር ፡ እንደሰው ፡ ቢሆን ፡ ኖሮ
እንደ ፡ ሰው ፡ ቢያስብ ፡ ኖሮ
ኃጢአቴን ፡ ልናዘዝ ፡ ህሊናዬ ፡ ሲወቅሰኝ
ምህረትም ፡ ልማጠነው ፡ ደጅ፡ ባስጠናኝ
ውድቀቴ ፡ ሳይገደው ፡ ባላገጠ ፡ ፊቱ ፡ በጠቆረ
ፍቅሩ ፡ ቀዝቅዞብኝ ፡ ድምጹ ፡ በሻከረ

እንኳንስ ፡ ልጁ ፡ ሊያረገኝ
ሥሙን ፡ ለመጥራት ፡ ባስከፈለኝ (፪x)
እንኳንስ ፡ ቤቱ ፡ ለመኖር
ከደጁ ፡ መጣል ፡ በተሳነኝ
ከደጁ ፡ መጣል ፡ በናፈቀኝ

አዝ፦ ግን ፡ እግዚአብሔር ፡ እንደሰው ፡ አይደለም
ከቶ ፡ እግዚአብሔር ፡ እንደሰው ፡ አይደለም
ምህረት ፡ ቸርነቱ ፡ ወሰን ፡ ቁጥር ፡ የለው
ከወዳጅም ፡ ወዳጅ ፡ ፍቅሩ ፡ ብዙ ፡ ነው
እግዚአብሔር ፡ እንደ ፡ ሰው ፡ እንደ ፡ ሥጋ ፡ ለባሽ
የወደቀን ፡ አይቶ ፡ እንዳላየ ፡ አይሸሽ

እንደ ፡ ሰው ፡ አይደለም (፬x)
እንደ ፡ ሰው ፡ አይደለም ፡ ፍቅሩ ፡ አያረጅም
እንደ ፡ ሰው ፡ አይደለም ፡ አይለዋወጥም
እንደ ፡ ሰው ፡ አይደለም ፡ ፍቅሩ ፡ አያረጅም
እንደ ፡ ሰው ፡ አይደለም ፡ አይለዋወጥም

እግዚአብሔር ፡ እንደ ፡ ሰው ፡ ቢያይ ፡ ኖሮ
እንደ ፡ ሰው ፡ ቢያስብ ፡ ኖሮ
ያለኝን ፡ ሁሉ ፡ ሳጣ ፡ ሲጐድል ፡ ሙሉ ፡ ቤቴ
ከንፈር ፡ ቢመጥልኝ ፡ ርቆ ፡ ከአጠገቤ
ባሕሪው ፡ ተለውጦ ፡ ቀስ ፡ እአለ ፡ በሽሽ ፡ በራቀ
ወዳጅነት ፡ ቀርቶ ፡ አዛኝ ፡ በመሰለ

ነፍሴን ፡ ሲከፋት ፡ ዝም ፡ ስል
ሃዘኔ ፡ ንቀት ፡ ቢመስል (፪x)
ውስጤ ፡ ማቅ ፡ ለብሶ ፡ ከሰው ፡ ቢያርቅ
እንደኮራሁ ፡ ቢያስበኝ ፡ እንደተኩራራሁ ፡ ቢያስበኝ

አዝ፦ ግን ፡ እግዚአብሔር ፡ እንደሰው ፡ አይደለም
ከቶ ፡ እግዚአብሔር ፡ እንደሰው ፡ አይደለም
ምህረት ፡ ቸርነቱ ፡ ወሰን ፡ ቁጥር ፡ የለው
ከወዳጅም ፡ ወዳጅ ፡ ፍቅሩ ፡ ብዙ ፡ ነው
እግዚአብሔር ፡ እንደ ፡ ሰው ፡ እንደ ፡ ሥጋ ፡ ለባሽ
የወደቀን ፡ አይቶ ፡ እንዳላየ ፡ አይሸሽ

እንደ ፡ ሰው ፡ አይደለም (፬x)
እንደ ፡ ሰው ፡ አይደለም ፡ ፍቅሩ ፡ አያረጅም
እንደ ፡ ሰው ፡ አይደለም ፡ አይለዋወጥም
እንደ ፡ ሰው ፡ አይደለም ፡ ፍቅሩ ፡ አያረጅም
እንደ ፡ ሰው ፡ አይደለም ፡ አይለዋወጥም