Eyerusalem Negiya/Qen Sale/Bemewedew Zeima

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ

ምሥጋና ፡ ልሰዋ ፡ በተዋበ ፡ ዜማ ሁሉ ፡ በሚቀለው ፡ ሊዘምር ፡ ከእኔ ፡ ጋር ደስ ፡ ብሎኝ ፡ ተነሳሁ ፡ ልመታ ፡ ከበሮ አምላኬ ፡ አርቆታል ፡ የልቤን ፡ እሮሮ

አዝ፦ (ኦሆኦሆሆ) ደስ ፡ ያለው ፡ ይዘምር
(ኦሆኦሆሆ) ተሰብሮለት ፡ ቀንበር
(ኦሆኦሆሆ) ይሰዋ ፡ ምሥጋና
(ኦሆኦሆሆ) ለጌታ ፡ እንደገና
ላከበረኝ ፡ ጌታ ፡ በምወደው ፡ ዜማ
በሚገባኝ ፡ ቋንቋ ፡ ቅኔን ፡ በሙገሳ
ምቱልኝ ፡ ከበሮ ፡ የታለ ፡ ዕልልታ
በማዕረግ ፡ መዝሙር ፡ ላክብረው ፡ በሆታ

የባርያዪቱን ፡ ውርደት ፡ አምላኳ ፡ አየና ስድብ ፡ ነቀፋዋን ፡ አስቦ ፡ እንደገና እግዚአብሔር ፡ ከሰማይ ፡ ቀንን ፡ ሲቆጥርላት መገፋቷን ፡ አይቶ ፡ ዛሬ ፡ ደረሰላት ቀንዴ ፡ ከፍ ፡ ብሏል ፡ አፌም ፡ ይዘምራል ጓዳዬ ፡ በቅኔ ፡ በዝማሬ ፡ ደምቋል

አዝ፦ (ኦሆኦሆሆ) ደስ ፡ ያለው ፡ ይዘምር
(ኦሆኦሆሆ) ተሰብሮለት ፡ ቀንበር
(ኦሆኦሆሆ) ይሰዋ ፡ ምሥጋና
(ኦሆኦሆሆ) ለጌታ ፡ እንደገና
ላከበረኝ ፡ ጌታ ፡ በምወደው ፡ ዜማ
በሚገባኝ ፡ ቋንቋ ፡ ቅኔን ፡ በሙገሳ
ምቱልኝ ፡ ከበሮ ፡ የታለ ፡ ዕልልታ
በማዕረግ ፡ መዝሙር ፡ ላክብረው ፡ በሆታ

የእንባ ፡ ስቅታዬ ፡ መርዶ ፡ በወጣበት ዛሬ ፡ ግን ፡ ከቤቴ ፡ ምሥጋናን ፡ ሞላበት አምላኬ ፡ በክብሩ ፡ ወደ ፡ እልፍኜ ፡ ገብቷል የዕልልታዬ ፡ ድምጽ ፡ ከሩቁ ፡ ይጠራል ወዳጅ ፡ ዘመዶቼ ፡ ጌታ ፡ ይሰራልኝን አይተው ፡ ከእኔ ፡ ጋራ ፡ አከበሩት ፡ ውዴን

አዝ፦ (ኦሆኦሆሆ) ደስ ፡ ያለው ፡ ይዘምር
(ኦሆኦሆሆ) ሆኖ ፡ ከእኒ ፡ እጋራ
(ኦሆኦሆሆ) የተደረገለት
(ኦሆኦሆሆ) እስቲ ፡ ማን ፡ አለና
ላከበረኝ ፡ ጌታ ፡ በምወደው ፡ ዜማ
በሚገባኝ ፡ ቋንቋ ፡ ቅኔን ፡ በሙገሳ
ምቱልኝ ፡ ከበሮ ፡ የታለ ፡ ዕልልታ
በማዕረግ ፡ መዝሙር ፡ ላክብረው ፡ በሆታ
ልስገድ ፡ በሽብሸባ ፡ ይጨመር ፡ ጭብጨባ
ይህ ፡ አይበቃምና ፡ መቅደስ ፡ ውስጥ ፡ ስገባ
ምቱልኝ ፡ ከበሮ ፡ የታለ ፡ ዕልልታ
በማዕረግ ፡ መዝሙር ፡ ላክብረው ፡ በሆታ (፪x)

</poem> }}