በምወደው ፡ ዜማ (Bemewedew Zeima) - ኢየሩሳሌም ፡ ነጊያ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ኢየሩሳሌም ፡ ነጊያ
(Eyerusalem Negiya)

Eyerusalem Negiya 2.jpg


(2)

ቀን ፡ ሳለ
(Qen Sale)

ዓ.ም. (Year): ፳ ፻ ፬ (2012)
ቁጥር (Track):

(5)


ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የኢየሩሳሌም ፡ ነጊያ ፡ አልበሞች
(Albums by Eyerusalem Negiya)

ምሥጋና ፡ ልሰዋ ፡ በተዋበ ፡ ዜማ
ሁሉ ፡ በሚቀለው ፡ ሊዘምር ፡ ከእኔ ፡ ጋር
ደስ ፡ ብሎኝ ፡ ተነሳሁ ፡ ልመታ ፡ ከበሮ
አምላኬ ፡ አርቆታል ፡ የልቤን ፡ እሮሮ

አዝ፦ (ኦሆኦሆሆ) ደስ ፡ ያለው ፡ ይዘምር
(ኦሆኦሆሆ) ተሰብሮለት ፡ ቀንበር
(ኦሆኦሆሆ) ይሰዋ ፡ ምሥጋና
(ኦሆኦሆሆ) ለጌታ ፡ እንደገና
ላከበረኝ ፡ ጌታ ፡ በምወደው ፡ ዜማ
በሚገባኝ ፡ ቋንቋ ፡ ቅኔን ፡ በሙገሳ
ምቱልኝ ፡ ከበሮ ፡ የታለ ፡ ዕልልታ
በማዕረግ ፡ መዝሙር ፡ ላክብረው ፡ በሆታ

የባርያዪቱን ፡ ውርደት ፡ አምላኳ ፡ አየና
ስድብ ፡ ነቀፋዋን ፡ አስቦ ፡ እንደገና
እግዚአብሔር ፡ ከሰማይ ፡ ቀንን ፡ ሲቆጥርላት
መገፋቷን ፡ አይቶ ፡ ዛሬ ፡ ደረሰላት
ቀንዴ ፡ ከፍ ፡ ብሏል ፡ አፌም ፡ ይዘምራል
ጓዳዬ ፡ በቅኔ ፡ በዝማሬ ፡ ደምቋል

አዝ፦ (ኦሆኦሆሆ) ደስ ፡ ያለው ፡ ይዘምር
(ኦሆኦሆሆ) ተሰብሮለት ፡ ቀንበር
(ኦሆኦሆሆ) ይሰዋ ፡ ምሥጋና
(ኦሆኦሆሆ) ለጌታ ፡ እንደገና
ላከበረኝ ፡ ጌታ ፡ በምወደው ፡ ዜማ
በሚገባኝ ፡ ቋንቋ ፡ ቅኔን ፡ በሙገሳ
ምቱልኝ ፡ ከበሮ ፡ የታለ ፡ ዕልልታ
በማዕረግ ፡ መዝሙር ፡ ላክብረው ፡ በሆታ

የእንባ ፡ ስቅታዬ ፡ መርዶ ፡ በወጣበት
ዛሬ ፡ ግን ፡ ከቤቴ ፡ ምሥጋናን ፡ ሞላበት
አምላኬ ፡ በክብሩ ፡ ወደ ፡ እልፍኜ ፡ ገብቷል
የዕልልታዬ ፡ ድምጽ ፡ ከሩቁ ፡ ይጠራል
ወዳጅ ፡ ዘመዶቼ ፡ ጌታ ፡ ይሰራልኝን
አይተው ፡ ከእኔ ፡ ጋራ ፡ አከበሩት ፡ ውዴን

አዝ፦ (ኦሆኦሆሆ) ደስ ፡ ያለው ፡ ይዘምር
(ኦሆኦሆሆ) ሆኖ ፡ ከእኒ ፡ እጋራ
(ኦሆኦሆሆ) የተደረገለት
(ኦሆኦሆሆ) እስቲ ፡ ማን ፡ አለና
ላከበረኝ ፡ ጌታ ፡ በምወደው ፡ ዜማ
በሚገባኝ ፡ ቋንቋ ፡ ቅኔን ፡ በሙገሳ
ምቱልኝ ፡ ከበሮ ፡ የታለ ፡ ዕልልታ
በማዕረግ ፡ መዝሙር ፡ ላክብረው ፡ በሆታ

ልስገድ ፡ በሽብሸባ ፡ ይጨመር ፡ ጭብጨባ
ይህ ፡ አይበቃምና ፡ መቅደስ ፡ ውስጥ ፡ ስገባ
ምቱልኝ ፡ ከበሮ ፡ የታለ ፡ ዕልልታ
በማዕረግ ፡ መዝሙር ፡ ላክብረው ፡ በሆታ (፪x)