ውለታው (Weletaw) - ኤፍሬም አለሙ

From WikiMezmur, the free amharic mezmur lyrics database.
ዘልለው ለመሔድ፦ የማውጫ ቁልፎች, ፍለጋ
ኤፍሬም አለሙ
(Ephrem Alemu)

Ephrem Alemu 2.png


(2)

ዝናዬ
(Zenayie)

ዓ.ም. (Year): 2009
ቁጥር (Track):

(8)


ሌሎች ፡ የአልበሙ ፡ መዝሙሮች
(Other Songs in the Album)
የኤፍሬም አለሙ ፡ አልበሞች
(Albums by Ephrem Alemu)

 
አዝ:- ኧረ ፡ እንዴት ፡ ነው ፡ ውለታው ፡ የእርሱ ፡ ፍቅር
እንዴት ፡ ብዬ ፡ ኧረ ፡ እኔስ ፡ እንዴት ፡ ልናገር (፪x)
እጅግ ፡ በዛ ፡ ውለታው ፡ ከአእምሮዬ ፡ በላይ ፡ ነው(፪x)

አዝ:- ኧረ ፡ እንዴት ፡ ነው ፡ ውለታው ፡ የእርሱ ፡ ፍቅር
እንዴት ፡ ብዬ ፡ ኧረ ፡ እኔስ ፡ እንዴት ፡ ልናገር (፪x)
እጅግ ፡ በዛ ፡ ውለታው ፡ ከአእምሮዬ ፡ በላይ ፡ ነው(፪x)

እጅና ፡ እግሩን ፡ ጐኑን ፡ በጦር ፡ የተወጋው
እጅና ፡ እግሬ ፡ ሰውነቴ ፡ ጤነኛ ፡ እንዲሆን ፡ ነው
የሾህ ፡ አክሊል ፡ ደፍቶ ፡ በመስቀል ፡ የዋለው
እጅና ፡ እግሬ ፡ ሰውነቴ ፡ ጤነኛ ፡ እንዲሆን ፡ ነው (፪x)

አዝ:- እጅግ ፡ በዛ ፡ ውለታው ፡ ከአእምሮዬ ፡ በላይ ፡ ነው (፪x)

ተራራ ፡ ሸለቆ ፡ አቀበት ፡ ሲወጣ
የእኔን ፡ ስቃይ ፡ የኔን ፡ ውርደት ፡ ጌታ ፡ ወስዶልኝ ፡ ነው
በጅራፍ ፡ ሲገረፍ ፡ በጥፊ ፡ ሲመታ
የእኔን ፡ ስቃይ ፡ የኔን ፡ ውርደት ፡ ጌታ ፡ ወስዶልኝ ፡ ነው (፪x)

አዝ:- ኧረ ፡ እንዴት ፡ ነው ፡ ውለታው ፡ የእርሱ ፡ ፍቅር
እንዴት ፡ ብዬ ፡ ኧረ ፡ እኔስ ፡ እንዴት ፡ ልናገር (፪x)
እጅግ ፡ በዛ ፡ ውለታው ፡ ከአእምሮዬ ፡ በላይ ፡ ነው(፪x)

መስቀል ፡ ተሸክሞ ፡ እንዲያ ፡ ሲንገላታ
ኢየሱሴ ፡ ለኔ ፡ ብሎ ፡ በደዌ ፡ ተመታ
የሕማም ፡ ሰው ፡ ሆነ ፡ በዝቶበት ፡ አበሳ
ኢየሱሴ ፡ ለእኔ ፡ ብሎ ፡ በደዌ ፡ ተመታ (፪x)

አዝ:- እጅግ ፡ በዛ ፡ ውለታው ፡ ከአእምሮዬ ፡ በላይ ፡ ነው (፪x)

አዝ:- ኧረ ፡ እንዴት ፡ ነው ፡ ውለታው ፡ የእርሱ ፡ ፍቅር
እንዴት ፡ ብዬ ፡ ኧረ ፡ እኔስ ፡ እንዴት ፡ ልናገር (፪x)
እጅግ ፡ በዛ ፡ ውለታው ፡ ከአእምሮዬ ፡ በላይ ፡ ነው(፪x)

አዝ:- ኧረ ፡ እንዴት ፡ ነው ፡ ውለታው ፡ የእርሱ ፡ ፍቅር
እንዴት ፡ ብዬ ፡ ኧረ ፡ እኔስ ፡ እንዴት ፡ ልናገር (፪x)
እጅግ ፡ በዛ ፡ ውለታው ፡ ከአእምሮዬ ፡ በላይ ፡ ነው(፪x)