From WikiMezmur: Mezmur Lyrics
እረጅሙን ፡ ጐዳና ፡ በጽድቅ ፡ እንዳልሄድኩኝ
አንተን ፡ እንዳላሳዝን ፡ ፊትህ ፡ እንደማልኩኝ
ዛሬ ፡ ምነው ፡ ጠፋኝ ፡ አቅም ፡ አጠረኝኝ
እኔ ፡ ነኝ ፡ ጥፋተኛ ፡ እኔን ፡ እኔን ፡ ማረኝ
ዕንቁዬን ፡ ሜዳ ፡ ጥዬው ፡ ብቻዬን ፡ ቀረሁኝ
ጌታ ፡ ሆይ ፡ መልሰኝ ፡ ምህረት ፡ አድርግልኝ
አዝ፦ መልሰኝ ፡ ወደድሮዬ ፣ መልሰኝ ፡ ወዳስተማርከኝ
መልሰኝ ፡ ወደጓዳዬ ፣ መልሰኝ ፡ ወደነገርከኝ
አንተን ፡ ተጣልቼ ፡ እንዴት ፡ እሆናለሁ
ከአንተ ፡ ተስማምቼ ፡ እኔስ ፡ እኖራለሁ
ስታበይ ፡ ገሥጸኝ ፡፡ ሳጠፋ ፡ ቅጣኝ
መንፈስህን ፡ ከእኔ ፡ አትውሰድብኝ
አንተ ፡ ዝም ፡ ካልከኝ ፡ ምንስ ፡ ይውጠኛል
የአንተ ፡ ዝምታ ፡ እኮ ፡ አፍ ፡ አለው ፡ ያወራል
ብቻ ፡ ይሁን ፡ እንጂ ፡ የነገርከኝ ፡ ኢየሱስ ፡ ያልከኝ
እኔስ ፡ ከሃሳብህ ፡ ጋር ፡ እስማማለሁ ፡ ይሁን ፡ እንዳልከኝ (፪x)
ብዙ ፡ የለፋሁበት ፡ ያከማቸሁት ፡ ሃብቴ
ከእጄ ፡ ላይ ፡ ተበተነ ፡ ሳላውቀው ፡ ከጥማቴ
የተቀደስኩለት ፡ ከዳኝ ፡ ማንነቴ
አወይ ፡ አለመታዘዝ ፡ አሻፈረኝ ፡ ማለቴ
አይረባህም ፡ ስትለኝ ፡ አንተን ፡ አለመስማቴ
ዛሬ ፡ ግን ፡ ገብቶኛል ፡ አድሰኝ፡ አባቴ
አዝ፦ መልሰኝ ፡ ወደድሮዬ ፣ መልሰኝ ፡ ወዳስተማርከኝ
መልሰኝ ፡ ወደጓዳዬ ፣ መልሰኝ ፡ ወደነገርከኝ
አንተን ፡ ተጣልቼ ፡ እንዴት ፡ እሆናለሁ
ከአንተ ፡ ተስማምቼ ፡ እኔስ ፡ እኖራለሁ
ጴጥሮስ፡ ሓዋርያው ፡ አልክድህም ፡ ያለው
ዶሮ ፡ ሳይጮህ ፡ በፊት ፡ ሶስት ፡ ጊዜ ፡ ነው ፡ የካደው
ነገር ፡ ግን ፡ ምህረትህ ፡ እጅግ ፡ ስለበዛ
አስበህ ፡ ለወጥከው ፡ ሰው ፡ አደረከው ፡ ጌታ
ብቻ ፡ ይሁን ፡ እንጂ ፡ የነገርከኝ ፡ ኢየሱስ ፡ ያልከኝ
እኔስ ፡ ከሃሳብህ ፡ ጋር ፡ እስማማለሁ ፡ ይሁን ፡ እንዳልከኝ (፪x)
|